SlideShare a Scribd company logo
1 of 16
Download to read offline
ዘኢትዮጵያ

Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82. Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

DC Mayor: 30 percent of African populations are from Ethiopia

Birtukan Mideksa Page 11

“Ethiopian represents the largest African population in the District of
Colombia, 30 percent of the African population is from Ethiopia. I can tell
you that 30 percent of population is vibrant, vital, active, and engaged,
Page 8
business leaders, are very involved in basic fabrics of our city.”
Mayor Vincent C. Gray noted during his opening remarks at DC Addis Sister City Agreement ceremony

የቀድሞ የኢት ጠቅላይ ሚኒስትር
ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ መጽሐፍ ወጣ
"እኛና አብዮቱ የሚለውና" የደርግን አፈጣጠርና የዘመኑን ታሪክ በዝርዝር
የሚያወሳው መጽሐፍ ትላንት ጀምሮ ገበያ ላይ መዋሉን አሳታሚው የፀሐይ
አሳታሚና አከፋፋይ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ወንድሙ
ለዘኢትዮጵያ ገልጸዋል። 450 ገጾች ያሉትን የሻምበል ፍቅረሥላሴ
ወግደረስን መጽሐፍ ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ በመጠኑ ቃኝቶታል።

“ደርግ ባከናወናቸው ተግባሮች
ወይም ባሳለፋቸው ውሳኔዎች
በብዙዎቹ ላይ ተሳታፊ ከመሆኔም
ባሻገር በዋናነት አብዮቱን ከመሩት
የደርግ አባላት ውስጥ አንዱ
ስለነበርኩኝ የደርግን ታሪክ ለመጻፍ
ስነሳ ራሴን እንደዋና ምንጭ አድርጌ
ወሰድኩኝ።... ከእስር ቤት ባልደረቦቼ
በጽሑፍና በቃል እየወሰድኩ እኔ
ከማስታውሳቸውና ከማውቃቸው
ጋር በማገናዘብ ይህንን መጽሐፍ
ለማዘጋጀት በቃሁ።”
ገጽ 5

Mrs. Obama challenged
the students to emulate
Menbere's story

With its network of
supporters worldwide,
Amnesty’s potential to
secure Eskinder’s freedom
is significant,.. The support
we get as political prisoners
is indispensible.”

202 518 0245
P.o.box 2049,
Fairfax, VA 22031
www.zethiopia com
dereje@zethiopia.com

ሰው ወደደም ጠላም ህወሓት መለስ ከነበረበት
የበለጠ ጠንካራ ሆን ይቀጥላል
አቶ ስብሐት ነጋ

ገጽ 2

በእዚህ በኩል

First lady Michelle Obama, left, Bell Multicultural High
School alumni , Ethiopian American Menbere, Assefa, center,
and Education Secretary Arne Duncan look to an audience
member asks a question at Bell Multicultural High School in
Washington, Tuesday, Nov. 12, 2013. First lady Michelle Obama
spoke to students about committing to education to create a
better future for themselves and their country. (AP
Page 11
Photo/Carolyn Kaster)

ተመድ- የአዲስ አበባ ህዝብ ከ10
ዓመት በኋላ 12 ሚሊዮን ይገባል
ገጽ 4

የዲሲ መንግሥት ባለታክሲዎችን እያማረረ ነው
የሕብረተሰባችን ምሶሶ የሆኑትን በርካታ የታክሲ ባለቤቶችና አሸከርካሪዎችን እየተጫነ ያለው የዲሲ መንግሥት (ታክሲ ኮሚሽን) አዳዲስ ደንቦችና አሠራር
አነጋጋሪ ከሆኑ ሰንብተዋል። ይህን አስመልከተው በግላቸው ጽሁፎችን በማቅረብ ሌሎችንም በማስተባበር በጉዳዩ ዙሪያ እየንተቀሳቀሱ የሚገኙትን አቶ ዓለሜ
ታደሰን ዘኢትዮጵያ አነጋግሯል። አቶ ዓለሜ በNPR እና WTOP ሬዲዮ በመቅረብ በታክሲ ነጂዎች በኩል ያለውን ብሶት በማሰማት የድርሻቸውን ለማድረግ
ሞክረዋል። የውል መፈረሚያው ቀን እንዲራዘም እስከ 500 ፊርማ አሰባስቦ በመጠየቅ ፣የታክሲ ካብ ኮሚሽኑ መረጃ አሰጣጡን በተሻለ መንገድ ለታክሲ
ነጂዎች እንዲያቀርብ በማስገደድ፣ መረጃውንም በText message እና በ dctg.org (DC taxi group) ድረ ገጽ ሀሳብና መረጃ መለዋወጫ እንዲሆን ጥረት
አድርገዋል። በአብዛኛው በሳቸው ከተነገረንና ከሌሎቹም ያጠናቀርነውን አስተያየት እነሆ አቅርበነዋል።
ገጽ 4

ቴዎድሮስ ምትኩ
አረፈ
በሙዚቃ የተቀነባበሩ እውቅ ዜማዎችን ሲያስደምጥ
የኖረው የሳክስፎን ተጫዋቹ ቴዎድሮስ ምትኩ
ዲሴምበር 22 ህክምናውን ሲከታተልበት በነበረው
በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ከዚህ ዓለም በሞት
ተለይቷል። በግል እኔና አንቺ፣ አማሌሌ፣ እሹሩሩና
የመሳሰሉትን ዜማዎች በአልቶ ሳክስ አሳምሮ
የተጫወተው ቴዎድሮስ ምትኩ፣ ከ1960ዎቹ ጀምሮ
በሙዚቃው ዓለም የኖረ ነው። ከእነ አለማየሁ እሸቴ
ጋር በሶሌክስ ባንድ ኋላም ደመራ ባንድን

የዶክተር
አምሳሉ
አክሊሉ
ቀብር
ተፈጸመ

ጨምሮ ከተለያዩ የሙዚቃ ቡድኖች ጋር ተጫውቷል።
ጥላሁን ገሠሠንና አስቴር አወቀ እንዲሁም ከወንድሙ
ተሾመ ምትኩ ጋር ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ
በትንፋሹ ሲያዜም ኖሯል። በተለይም በቨርጂኒያ ባቲ
ሬስቶራንት የወንድሙ የተሾመ ምትኩን እነ ጋራ
ሥር ነው ቤትሽ፣ ሞት አደላድሎ አፈር ሳይጫነኝ፣
የዘመዴ ባዳና ሰማይ ሲላወስ የመሳሰሉትን ዘመን
ተሽጋሪ ጣፋጭ ዜማዎችን አስውቧል። በተለይ
በ1987 አካባቢ ያወጣው በሙዚቃ መሳሪያና በሱ
ትንፋሽ ብቻ የተቀነባበረውን አልበሙ የትም መቼም
እሚደመጥ ሆኗል። ከአንጋፋው ጥላሁን ገሠሠ ጋር
እህትማማቾን ያገቡ ወዳጆች ሲሆኑ ከባለቤቱ ወ/ሮ
መዓዛ በዙ ጋር ከ20 ዓመታት በላይ በበትዳር አብረው
ኖረዋል።

ያልተወደደው ኑሮ ውድነት

እኚህ ሰው ካሁን በኋላ የሚያስለቅሱት እንጂ የሚያለቅሱለት ሰው ላይኖር
ይችላል። የዚህን እንባ ምንጭና ሚስጥር መመርመር ብቻውን አይበቃም።
መኮንኑ አልቅሰው ቀና ሲሉ ስለመጪው ምን ሊያስቡ እንደሚችሉም
መገመት ይገባል። ለዚያ ግምት የሚበቁ በቂ ምልክቶች አሉ። ምልክቶቹ
ምንድናቸው?
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ = ወታደራዊ ሓርነት ትግራይ (ወሓት?)
እየሆነ ይሆን? ድርጅቱ ህወሓት ቀድሞሞ "ህዝባዊ" አልነበረምና
ለትግራይ ህዝብ አይቆምም። ከትግራይ ግን ለድርጅቱ የሚቆሙ ተጠቃሚ
ዜጎችን አፍርቷል። እነዚያ ዜጎች ሲቪልም ይሁን ወታደር ካሁን በኋላ
ለድርጅታቸው ዘብ ይቆማሉ። ወታደሮች ይሆናሉ። ይማራሉ፣ ይሰለጥናሉ፣
ይነግዳሉ፣ ይበለጽጋሉ በሁሉም ዘርፍ ብቃት ባለው መልክ ይደራጃሉ።
በፍጹም ይሉኝታ አይኖራቸውም። የላቁት ወታደራዊ ማዕረጎች በሙሉ
የእነሱ ይሆናሉ።
ከወታደሩም ወደ ሲቪል መ/ቤቶች ተመድቦ መዛወር ይቻላል ተብሏል።
ለዚህ ሲባል ቀጭን ትዕዛዝ ይወጣል። ህገመንግሥቱ ለነሱ ተብሎ ይለወጣል።
አዋጆች ይወጣሉ። ልዩ በጀቶች ይፀድቃሉ። በዚያች አገር ያለነሱ ማንም
እንደሌለ የአምሳና የመቶ ዓመት እቅድ ያወጣሉ። ይህን ኃላፊነት በበላይነት
ለመምራት መለስ ዜናዊ ለራሳቸው ሲሉ አደራጅተውት የሄዱት ሠራዊት
እየተነቀሳቀሰ ነው። የመጀመሪያ ዓላማው ወታደራዊ መንግሥት መሆን
ነው። እስካሁን ካልሆነ ማለት ነው። ሠራዊቱ የራሱ ምክር ቤት መሳይ፣
የራሱ ደህንነት፣ የራሱ ፖሊስ፣ ፣ የራሱ የቴሌኮሙኒኬሽንና የራሱ የቢዝነስ
ተቋም እያቋቋመ ፣ የልማት መርሃ ግብሮችን እያወጣ ይመስላል። የፖለቲካ
ድርጅቱ ሳስቶ እሱ እየፋፋ ነው።
ገጽ 2

የኢትዮጵያውያን እንባ!

በእንግሊዝኛ-አማርኛ መዝገበ
ቃላት መጽሐፋቸው የሚታወቁት
ዶክተር አምሳሉ አክሊሉ የቀብር
ሥነ ሥርዓት በየካ ቅዱስ ሚካኤል
ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
አማርኛ፣ ግእዝ፣ እንግሊዝኛ፣
አረብኛ፣ ጀርመንኛ፣ ጣሊያንኛና
እብራይስጥ
ቋንቋዎችን
አቀላጥፈው የሚናገሩት ዶክተር
አምሳሉ፤ የእንግሊዝኛ-አማርኛ
መዝገበ ቃላት፣ የጀርመንኛአማርኛ መዝገበ ቃላት፣ የአማርኛ
ፈሊጦች፣ አጫጭር ልቦለዶች፣
“ጥሩ የአማርኛ ድርሰት እንዴት
ያለነው?” የመሳሰሉት ለህትመት
አብቅተዋል።
”የኢትዮጵያ
ገጽ 9

ግ ፉ ገ ና ነው!

“ኑሮ ተወዷል” ያልተባለበት ቀንና ዓመትን ለማስታወስ ከማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። ግን ሰው እየኖረ ነው!
ምንድነው ተአምሩ? ሰው እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ለጊዜው ማወቁ ይቸግር ይሆናል። መንግሥት የሚያደርገውን
ግን መመልከት ይቻላል። መንግሥት ምን እያደረገ ነው? የሚያደርገውንስ እስከመቼ ያደርገዋል? ህዝቡ ግን
ኑሮውን እየገፋ ኑሮውም እሱን እየገፋው ነው።
ገጽ 14

ገጽ 7
ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

ግብፅን ወሓት?
ያየ!
ህወሓት ወደ
(ወታደራዊ ሓርነት ትግራይ)

2

ጄነራሎቹ
ሥልጣን
ገንዘብ
ጠመንጃ

"መለሾ
ድርጅቱን
አልገደለውም
በህይወቱ ነው
ያለው ግን

ይጠነክራል!"

አቶ ስብሐት ነጋ

የአቶ መለስ ሞት በተሰማበት ምሽት አቶስብሐት ሥልጣን ላይ ከሌሉ ተራ አባል ከሆኑ በየትኛው ኃላፊነታቸው
ነው ወደ ደህንነት ጽ/ቤት ሮጠው የሄዱት? ሥራ አስፈጻሚው ስብሰባው ላይ የተገኙት? ወይ ያሉት ነገር ልክ
አይደለም? ወይ እንዳሉት ተራ አባል አይደሉም። ከሁለት አንዱ ልክ አይመስልም። ወይም ሁለቱም ውሸት ሊሆን
ይችላል። ወይስ እንደሚባለው ሌላ ስውር መዋቅር አለ ማለት ነው? 34 ጄኔራሎችን ሹሞያደረው ዓይነት መዋቅር?

ከመለስ ሞት በኋላ ሥልጣን እየተቆለላቸው ከጠ/ሚኒስትሩም በላይ እየሆኑ ያሉት ጠ/ ኤታማዦር ሹሙ
ጄ/ል ሳሞራ በቻይና

የጠ/ሚኒስትሩን ዝቅ የጠ/
ኤታማዦር ሹም ሥልጣንና
ተግባርን ደግሞ ከፍና ለየት
ባደረገው የሰሞኑ አዲሱ አዋጅ
አማካይነት እነዚህ ተፈጻሚነት
ይኖራቸዋል፦
ከጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ሥልጣናት
1.	

የመከላከያ አዛዦች ካውንስልን ይሰበስባል፣ ሥራዎቹን
ያስተባብራል፣ የውሳኔዎቹን ተግባራዊነት ይቆጣጠራል

2.	 የጦር ኃይሎች ጠቅላይ መምርያን በበላይነት ይመራል፣
3.	 የአገር መከላከያ ሠራዊትን ያደራጃል፣ ሠራዊቱን በማንኛውም
ጊዜ ለውጊያ ብቁና ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
4.	 የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ (ጠቅላይ ሚኒስትሩ) መመርያና
ውሳኔን መሠረት በማድረግ ሠራዊቱን ያዛል፣ ያዋጋል፣
5.	 ጠ/ ሚኒስትሩንና የመከላከያ ሚኒስትሩን በወታደራዊ ጉዳዮች
ላይ ያማክራል፡፡ (4ኛውን ይህ ይቃረነዋል የታዛዥ አማካሪ?)
6.	 ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ድምፅ የመስጠት መብት
የማይኖራቸው የሠራዊቱ ልዩ ልዩ አዛዦች በካውንስሉ ስብሰባ
እንዲሳተፉ የማድረግ ሥልጣንን ይኖረዋል፡፡ (የካውንሱሉ
አባላት በሠራዊቱ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ዕዞች ዋና አዛዦች፣
የአየር ኃይል ዋና አዛዥና የፕሪንሲፓል ስታፍ ዋና ኃላፊዎች፣
የአዛዦች ካውንስል አባላት ናቸው።)
7.	 የወታራዊ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት ለካውንሱሉ አቅርቦ
ያስፀድቃል፡፡

“አብሬያቸው ጎልፍ ክለብ ስጫወት እውላለሁ” ስለሚሉት ሿሚና ተሿሚ ጀኔራሎች ሹመት አቶ ስብሐት
አለማወቃቸው ያስገርማል። ተከትሎ የሚመጣባቸውን ጥያቄ ከመጋፈጥ ይህን አለማወቅ የሚያዋጣ ሆኖላቸዋል።
መንግሥት ተጠሪነቱን ለመከላከያ ሚኒስቴር አድርጎ በአዋጅ ያቋቋመውን ወታደራዊ የቢዝነስ ኢምፓየር
ስብሐት ወታደራዊ ሳይሆን ሲቪል መሆኑን ተናግረዋል። “እንዲህ ያለ ልዩነት ቢኖርማ ድርጅቱ ለምን እለቃለሁ
ለማስተካከል ድርጅቱ ውስጥ እቆይ ነበር” ካሉ በኋላ ወረድ ብለው ደግሞ “እንዲህ ያለ ልዩነት ካለማ ለምን
እቆያለሁ ድርጅቱን እለቅ ነበር አሁንም ከድርጅቱ አልወጣሁም... ያሉበትን የአቶ ስብሐት ነጋን የዘኢትዮጵያ
ጋዜጣ ቃለ መጠይቅ በከፊል ከወራት በፊት በድህረ ገጾች አስደምጠነዋል። ጥያቄ አይፈሩም የሚባሉት ስብሐት
ያመኑበትን መልሰው ካልመሰላቸውም ክደው ካልሆነላቸውም የጠያቂውን ሰዓት ቆርጠው መገላገል የሚችሉ
ናቸው። ለተቃዋሚቻቸው ሲሆን ነገራቸው ፊት ለፊት ነው። ጥላቻቸውን አይደብቁም። ስለቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ
ያላቸውን ጥላቻ ቂም ባልረበደ ቁጣቸው ገልጸዋል። ስለ አቶ መለስና ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ ግን ቀለል ያለ
የውስጥ ጠብ ነው ዓይነት አመላለስ ተጠቅመዋል። ስለ ኢትዮጵያ ታሪክም አንጻር የሚያውቁትን ባይሆንም
የሚያምኑበትን በመናገር ደፋር ናቸው። በቃለመጠይቁ ወቅት ለምሳሌ እንዲህ ብለዋል "ከታሪክ አንጻር ስናየው
እንደገና ይታይና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያስተካክለው የታሪክ ቴስት ያለው (ከህወሓት ሌላ) ማነው? በኢትዮጵያ
የነበረውን የታሪክ ተቃርኖ (ኮንትራዲሽን) ማን አወጣው? ለማመን የማይፈልግ ግን ይህን ለማየት የማይፈልግ
ብቻ ሳይሆን ለማየት አይችልም። አሁን መስፍን ወልደማርያም ህወሓት ኢትዮጵያዊ ነው ሊል አይችልም። አቅም
የለምው። ማንበብ አይችልም....ምክንያቱም ታሟል!
አቶ ስብሐት የተዳከመውን ድርጅታቸውንና ፈርጥሞ የወጣውን ሠራዊታቸውን በማግባባትና በመሸምገል ሥራ
መጠመዳቸው ይነገራል።

ከስብሐት ነጋ ቃለ
መጠይቅ በከፊል
ዘኢትዮጵያ - ወደ አሜሪካ ለምን መጡ ?
አቶ ስብሐት- ወርልድ ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ
ዓመታዊ በዓል አለ፡፡ ለዚያ ነው የመጣሁት።

አቶ ስብሐት- ወረቀት ጽፌኮ ነው! ወረቀት
ጽፌ የአሁን ማዕከላዊ ኮሚቴ ምርጫ
እጩነት አልቀበልም። ተራ ሆኜ ለመታገል
ነው የምፈለገው ብዬ በእጄ የጻፍኩት ነው።
እና እኔ እዚያ ስለነበርኩ ማመልከቻ ጽፌ
ለአለቃ ጸጋዬና ቴዎድሮስ ሓጎስ..እና ሶስት ጊዜ
አመልክቼ ነበር ከዚያ በፊት አልተቀበሉትም።
ሶስት ጊዜ ጽፌ ነው በአራተኛው ተቀበሉት።
ዘኢትዮጵያ - መለስ እያሉ ማለት ነው?

ዘኢትዮጵያ - ማንን ወክለው ነው የመጡት ?

አቶ ስብሐት- አዎ!

አቶ ስብሐት- ውጋገን ባንክ የፕራይቬት ባንክ ነው።
እሱን ወክዬ ነው። የቦርዱ ቼር ማን ነኝ።

ዘኢትዮጵያ - ለምንድነው?

ዘኢትዮጵያ - የኢህአዴግ አባል ነዎት አሁን?
አቶ ስብሐት- የኢህአዴግ አባል የሚባል የለም
የኢህአዴግ አባል ድርጅት ነው፡፡ የሕወሃት አባል
ነኝ።
ዘኢትዮጵያ - በድርጅቱ ተራ አባል ነዎት? የአባልነት
ደረጃዎ ምንድነው?
አቶ ስብሐት- ተራ አባል ነኝ።
ዘኢትዮጵያ - እንግዲህ ድርጅቱን መሠረቱ
ከሚባሉት ሰዎች ነዎት በአንድ ወቅትም ድርጅቱን
በሊቀመንበርነት መርተዋል እየወረዱ መጥተው
አሁን ተራ አባል ነው የሆኑት፣ አወራረድዎ እንዴት
ነው?

አቶ ስብሐት- ስለዚህ ከዚያ በፊት
ያመለከትኳቸው በእድሜ ቢሆን ኖሮ ልወርድ
እችል ነበር።
ዘኢትዮጵያ - አዎ ግን መለስ እያሉ ነው
ከማዕከላዊ ኮሚቴ የወረዱት!
አቶ ስብሐት- አዎ በማመልከቻ ነው አንድ

ነው እነስዬ የወጡበትን? እነሱንም ጨምሮ?
አቶ ስብሐት- አዎ የተባረሩ ናቸው።
ዘኢትዮጵያ - እነስዬም....?
አቶ ስብሐት- አዎ መካፈፋል አይደለም።
እነሱኮ ተባረሩ! መባረር ነው። ሁል ጊዜ
የሚባረር አለ ደረጃው የሚቀንስ አለ። ስለዚህ
መከፋፈል የነበረው በ73 ዓመተ ምህርት
በኛ በነግድይ ዘር ዐጽዮን በነበረበት ጊዜ። ዘ
ኦንሊ ታይም ስለፕሮግራም ጥያቄ በህወሃት
ጥያቄ የተነሳ ያኔ ብቻ ነው። እንጂ ህወሃት
ከተፈጠረ ጀምሮ የፕሮግራም ጥያቄ አወዛጋቢ
ሆኖ አያውቅም። የሚከፋፍል የፕሮግራም
ጥያቄ ነው ወይም የአደረጃጀት ጥያቄ ነው።
ተቋሙ ማለት ነው። እና በአሠራር ደረጃም
በፕሮግራምም ብትል የሚከፋፍል ነገር
የለም። የሚከፋፍል ፕሮግራም ነው ሌላ ነገር
ሊመጣ አይችልም። እና ማንኛውም ሀሳብ
ልዩነት ሲመጣ በተራዘመ ሂደት ውይይት

"(TPLF) ህወሓት ሰው ወደደም
አልወደደም መለስ ከነበረበት በጣም
የጠነከረ ድርጅት ይሆናል።"
ስብሐት ነጋ

አቶ ስብሐት- በምርጫዬ ነው። ከሊቀመንበርነት
ጽፌ ማመልክቻ አቅርቤ ነው።
ዘኢትዮጵያ - ወይስ መተካካት በሚለው ነው?

8.	 ከውትድርና መሰናበት በሚገባቸው ወይም በፍላጎት
ስንብት በጠየቁ ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ጉዳይ በመወያየትና
የግለሰቦቹን አስተያየት ወይም ቅሬታ በማዳመጥ፣ የውሳኔ
ሐሳብ ለጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ለሆኑት ለጠቅላይ
ሚኒስትሩ ያቀርባል፡፡

አቶ ስብሐት- መተካካት አለ መተካከት ቢኖርም
የግድ ስትሪክት የሆነ በዚህ ዓመት ትወጣለህ የሚል
የለም። እኔ ሶስት ጊዜ አመልክቼ በአራተኛው ላይ....

9.	 (ከእንግዲህ የሠራዊቱ አባላትን ወደ ሲቪል የመንግሥት
መሥሪያ ቤቶች ማዛወር ይቻላል።) ዝውውሩ በአባሉ
ስምምነት ካልሆነም በግዳጅ (በኤታማዡር ሽሙ) ይፈጸማል።

አቶ ስብሐት- አይደለም ሊቀመበር የነበርኩት ድሮ
ነው።

10.	 ከዚህ ቀደም ያልነበሩ የወታደራዊ ዓቃቤ ሕግ፣ የወታደራዊ
ተከላካይ ጠበቃና የወታደራዊ ፖሊስ አደረጃጀቶችን መፍጠር
የሚያስችል አዳዲስ አንቀጾች ተካተዋል፡፡ የኤታማዦር ሹሙ
ሥልጣን እዚህም ላይ ከፍተኛ እንደሆነ ይገመታል።

ዘኢትዮጵያ - ሊቀመንበር በነበሩ ጊዜም ነው?

ዘኢትዮጵያ - ገባኝ ያኔ በምርጫ ነው የወረዱት
ከሊቀመንበርነቱ?

አረፍተ ነገርናትኮ!

አቶ ስብሐት- በድርጅቱ ባህል ወደ ሥልጣን
የሚመጣው በምርጫ ነው። ከተመረጠ ይመረጣል
ካልተመረጠ ደግሞ ይወድቃል ማለት ነው። እኔ
ተመርጬ ነው። ስወርድ ደግሞ በራሴ ነው በቃ
ብዬ ለምኜ ነው።

ዘኢትዮጵያ - የጻፉት? ምን የምትል ናት አንድ
አረፈተ ነገር ከሆነች በቃልዎ ያውቋታል!

ዘኢትዮጵያ - ለምን መልቀቅ ፈለጉ?

ዘኢትዮጵያ - ያንን ያደረጉት አለመስማማት
ስላለ ከድርጅቱ ጋር አንዳንድ ግጭቶች
ስለነበሩ ነው ወይስ ራስዎ የሰጡት ምክንያት
ነው ትክክለኛው?

አቶ ስብሐት- በቃ እየተኩ የመጡ ወጣቶች ከኔ
ይበልጣሉ። ያኔ መለስ ነበር መለስ ይሻላል ብዬ ተራ
የፖለት ቢሮ አባል ሆኜ ነው ለምኜ ነው በማመልቻ
ጠይቄ። አሁንም እንዲሁ ለአራተኛ ጊዜ አመልክቼ
ነው።
ዘኢትዮጵያ - አሁን ሲሉ አሁን የመጨረሻውን
2010 ላይ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቱ የወጡትን
ማለትዎ ነው?
አቶ ስብሐት- አዎ!
ዘኢትዮጵያ - ግን ይነገር የነበረው በመተካካቱ
መሠረት ነው። እርስዎ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎቹም አንድ
ስምንት የምትሆኑ ናችሁ ወጣችሁ የተባለው ያኔ።
አቶ ስብሐት- አይዶንት ኖ! (አላውቅም)
ዘኢትዮጵያ - እንደሱ ነው የተባለው።
አቶ ስብሐት- አዎ ሌሎቹም ወጥተዋል።
ዘኢትዮጵያ - ግን ለህዝቡ የተነገረው መተካካት
የሚል ነው የርስዎንም ጨምሮ። ስለዚህ እሱ
ኢንፎርሜሽን ልክ አልነበረም ማለት ነው? የእርስዎም
በፈቃደኝነት መሆኑ አልተገለጸም። እርስዎ ብቻ
ነዎት በፈቃደኝነት የወጡት ወይስ ሌሎቹም ናቸው?

አቶ ስብሐት- ነርኩህኮ “እኔ በአሁኑ ጉባኤ
የማዕከላዊ ኮሚቴ እጩነት አልካፈልም። ተራ
ሆኜ ለመታገል እፈልጋለሁ።”

አቶ ስብሐት- ያለመስማማትማ ቢኖር ኖሮኮ
እቆያለሁ በድርጅቱ ለምን እወጣለሁ? ያለ
መስማማት ሲኖር ያውም ትቆያለህ ስምምነት
ልታመጣ ትቆያለህ። ያለመስማማት አልፏል።
ከአንጃው ጋር የነበረ ማለት ነው። ስለዚህ
ባለመስማማት አይደለም። ፈልጌ የወጣሁት
ነው። ይሄኮ ሺ ጊዜ የተጻፈ ነው አዲስ ነገር
አይደለም።
ዘኢትዮጵያ - ስለዚህ አንዳንድ ጽሁፎች
እንደዚህ ይወጡ ነበር። በተለይ ከወ/ሮ አዜብ
ጋር በተያያዘ አለመስማማት ነበራቸው የሚል
ነገር። ከወ/ሮ አዜብ ጋር የነበርዎት ግንኙነት
ምን ይመስላል? ጤናማ ነው?
አቶ ስብሐት- አሁን ምንድነው መሰለህ፣
አንድ ነገር ከመጀመሪያው ልንገርህ። በ
TPLF (ህወሃት) መካፈፈል የሚባል ነገር
አጋጥሞ አያውቅም። TPLF has never been
divided!
ዘኢትዮጵያ - የመጨረሻውንም ጨምሮ ማለት

ይደረግበታል። ሶስት ዓመት ይፍጅ አራት
ዓመት ይፍጅ ...ይሄ መደባዊ ጥያቄ የሀብታም
ገበሬ የሚለው እሱም ግደይ ብቻውን ነው
የወጣው አንጃ የነበረው የፕሮግራም አይደለም
የሥልጣን ነው እሱም ተባረረ ዜር ፎር
መለያየት መከፋፈል የሚባል ነገር አጋጥሞም
አያውቅም። በ TPLF አይተን አናውቅም።
ሌሎችም ቢሆኑ የኢህአዴግ ድርጅቶች
መከፋፈል የሚባል ነገር አልነበረም። የሀሳብ
ልዩነት ግን አሁንም አለ። ብዙ የሀሳብ ልዩነቶች
ግጭቶች አሉ።
ዘኢትዮጵያ - ምናልባት በሰዎች መካከል
ያለውን ልዩነት ለማለት ነው። ሰዎች
ተከፋፍለው በፕሮግራም ግን አንድ ሊሆኑ
ይችላሉ። ፕሮግራሙ አንድ ሆኖ ሰዎች ግን
ተለያይተዋል። አይተናል። የድርጅት አመራር
የነበሩ ሰዎች....
አቶ ስብሐት- ይባረራሉ እና እኔ ልዩነት
አለኝ ብዬ አልወጣሁም፣ ከድርጅቱ ድርጅቱ
ውስጥኮ ነኝ ያለሁት። ልዩነት ቢኖርማ ስልጣን
ላይ እቆያለሁ። እንዲፈታ በመፍታት ላይ
ሚናዬን እንድጫወት። እኔ ድርጅቱን አምኜ
ተራ ሆኜ ብታገል ይሻለኛል።
ዘኢትዮጵያ - ስለዚህ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ተብሎ
የሚነገረው ነገር በተደጋጋሚ...
አቶ ስብሐት- አልሰማሁም እንደሱ ሰምቼ
አላውቅም።
ዘኢትዮጵያ -ከወ/ሮ አዜብ ጋር ችግር
አላቸው....
ወደ ገጽ 3
ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

ከአፍሪካ በእንስሳት 1ኛ የሆነች አገር
ቆዳ ከውጭ መግዛት ጀምራለች።

3

የአዲስ አበባ ሕዝብ ስንት ነው?

ተመድ- ከአስር ዓመት በኋላ

የከብትን አገር ቆዳ ቸገረው 12 ሚሊዮን ይገባል
ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር፣ ትገዛለች፣ አሁን ደግሞ የከብት ቆዳም ልትገዛ ነው!
ከአፍሪካ በእንስሳት ሀብት 1ኛ የሆነች አገር ቆዳ ከውጭ መግዛት ጀምራለች። የከብትን አገር ቆዳ ቸገረው
እንደማለት ነው። ደግሞ ይህን የሚለው ራሱ መንግሥት ነው።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያሉት የቆዳ ፋብሪካዎች በዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የበግና ፍየል ሌጦና ከ2
ሚሊየን በላይ የበሬ ቆዳ ይፈልጋሉ። እየቀረበላቸው ያለው ግን ከግማሽ በታች 17 ሚሊየን ሌጦና ከ1 ነጥብ
5 ሚሊዮን በታች የሆነ ቆዳ ሆኗል። በጥሬ ቆዳ አቅርቦትና ፍላጎት መካከል የ20 ሚሊዮን ክፍተት አለ::
በዚህ የተነሳ የቆዳ ፋብሪካዎች ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው ነው። የቡና ዋጋን መውደቅ በአለበት ሁኔታ
ኢትዮጵያ ተስፋ ያደረግችበት የቆዳና ሌጦ
ኤክስፖርትም ችግር እየመጣበት ነው።

በግና በሬ ሲወደዱ አራጅ
ጠፋ ቆዳው ከየት ይምጣ?

በዚህ የተነሳ ሃገሪቱ ከዘርፉ የምትጠብቀውን
ገቢ ማሳካት አስቸጋሪ መሆኑን የኢትዮጵያ
ቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስትቲዩት ዋና
ዳይሬክተር አቶ ወንዱ ለገሰ መግለጻቸውን
የመንግሥት ሚዲያዎች ሰሞኑን ዘግበዋል። ዋና ዳይሬክተሩ እንደሚሉት ቆዳ ፋብሪካዎቹ የሚፈልጉትን የጥሬ
ቆዳና ሌጦ አቅርቦት የሚያገኙት 20 በመቶውን ከቄራዎች የተቀረውን 80 በመቶ ደግሞ ከህብረተሰቡ ነው።
ህብረተሰቡ ደግሞ አቅቶታል። ከብት የሚያርደው በአመዛኙ የበዓል ወቅቶችን እየጠበቀ በመሆኑ አብዛኛዎቹ
የቆዳ ፋብሪካዎች አቅማቸውን ሙሉ ተጠቅመው መስራት እንዳይችሉ አድርጓል። በዚህም በእንስሳት ሃብቷ
ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነቸውን ሃገራችንን ተሻግረው ጥሬ ቆዳና ሌጦ ፍለጋ ወደ ውጭ ገበያ ማማተር ጀምረዋል ።
መንግሥት ግን እንደ ኢንደስትሪ ሚኒስትር ደኤታው አቶ ታደሰ ኃይሌ በመሳሰሉት ከፍተኛ ባለሥልጣናቱ
አማካይነት በሰጠው መግለጫ ማስተባበል የያዘ መስሏል። ይህ የሆነው በእንስሳቱ ላይ በሚደርሰው የጤና
ችግር እንጂ በኑሮ ውድነቱ አለ መሆኑን እየገለጸ ነው። ለፋብሪካዎቹ ከሚቀርበው ቆዳ ውስጥ 65 በመቶው
ጥራት የጎደለው በመሆኑ ይጣላል በሚል ጉዳዩን ከጥራትም ጋር አያይዞታል። በሃገሪቱ የተዘረጋው የግብይት
ስርዓት ከቆዳና ሌጦ ባለቤቶች ፋብሪካዎች ጋር እስኪደርስ ድረስ ከአራት በላይ የገበያ ሰንሰለቶችን በማለፉ
ቆዳውን ለብልሽት የሚዳርገው መሆኑንም የሚኒስትር ደኤታው መግለጫ አመልክቷል። ይህን ለመቅረፍ
ሲባልም የንግድ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን «የጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይት አዋጅ» አዘጋጅቶ
መጽደቁን እየተጠባበቀ መሆኑም ተገልጿል።
ለዘመናት የኖረው የገበያ ሰንሰለት እንደምን ሆኖ ቆዳውን ለድንግተኛ ብልሽት ሊያጋልጠው እንደቻለ ግን
የሚኒስትሩ መግለጫ አላብራራም። እንዲያውም በተቀራኒው መንግሥት ከፍተኛ ጥራት እንዳለው ከሚነገረው
ከኢትዮጵያ ቆዳና ሌጦ ላለፉት ዓመታት በዓመት 123 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ እያስገኘ መምጣቱን
በመግለጽ፣ በ2007 ዓመት መጨረሻ በዓመት 500 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢን ለማግኘት እቅድ መያዙን
ሲገልጽ መቆየቱ ይታወቃል። ይልቁንም ችግሩ የቆዳ ጥራት ሳይሆን እንደተባለው ህዝቡ በኑሮ ውድነት የተነሳ
ከብት ማረዱን እየቀነሰ በመጣቱ የመሆኑን ግምት ያጎላዋል። የሆኖ ሆኖ ኢትዮጵያው ወደ 30 ለሚደርሱ
የቆዳና ተያያዥ ፋብሪካዎቿ ቆዳንና ሌጦን ከውጭ ገዝታ ማስገባት ግዴታዋ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ ሁኔታዎችን
ማመቻቸት ጀምራለች።
በዚህ የተቆጩትን የሞጆ ቆዳ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ሬድዋን በዳዳ ለዘመን እንደገለጹት “በግ የሌላት
ሶማሊያ እንኳን የበግ ሌጦ ወደ ውጭ ትልካለች።” ብለዋል። አገር ውስጥ ገዢ ያጡ ነጋዴዎችም ከወትሮው
በላቀ ሁኔታ በግና ፍየሎችን በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ መንዳት መጀመራቸው ተሰምቷል። ጤፍ ኤክስፖርት
አድርጎ እንጀራን እንደማስመጣት መስሏል።

“The population of the capital Addis Ababa
has doubled every decade since 1984 and
UN-Habitat has predicted that the population
will reach 12 million in 2024. ... “ ይላል
አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል። (
የ The United Nations Human Settlements
Programme (UN–Habitat)። 2014 ማለት የዛሬ
10 ዓመት ማለት ነው። በመሆኑም ይህን አሳሳቢ
ችግር በጽኑ ልታስብበት እንደሚገባት የሚመክሩ
ዓለም አቀፍ ተቋማት እየተሰሙ ነው። የኢትዮጵያ
የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣንም 5 ሚሊዮን
አልፏል የሚባለውን የአዲስ አበባ ህዝብ ቁጥር
በድፍረት ባይቀበልም ሲፈራ ሲቸርም ቢሆን ስለ
አጨማመሩ ማሳሰቡ አልቀረም። ዙሪያ ጥምዙን ሄዶ
“የከተማ ህዝብ ቁጥር ዕድገት ወደፊትም እስካሁን
ከታየው ባላነሰ ፍጥነት የሚቀጥል መሆኑን ለመገመት
የሚያስችሉ መሰረታዊ መነሻዎች አሉ” ካለ በኋላ
“ እ.ኤ.አ. በ2020 ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ
መካከል 30% የሚሆነው በከተማ እንደሚኖር
ይገመታል” ብሏል።
ከተማ ማለት ምንድነው? አንድን ከተማ ከተማ
የሚያስብለው ከህዝብ ብዛት አንጻር ስንት ሰው
ሲኖርበት ነው የሚለውን መመለስ አስፈላጊ ነው።
ቤትና ሰው የሚቆጥረው ኤጀንሲው ግን አሁንም እሱን
በቀጥታ ከመመለስ ኢትዮጵያ ውስጥ “2ሺ እና ከዚያ
በላይ የህዝብ ብዛት ያላቸው ከተሞች 924 ናቸው”
ይላል። ቀበሌውን ሁሉ ከተማ እያልን እንዳንቸገር
ቢያንስ ከ100ሺ በላይ ነዋሪዎች ያሉባቸውን ከተሞች
እንዲነግረን ብንጠይቅ ከኤጄንሲው የምናገኘው 13
ከተሞች ብቻ መሆናቸውን ነው። እንደ ኤጄኒስው
ገለጻ ከአዲስ አበባ ቀጥላ በርካታ ነዋሪዎች ያሏት
ሁለተኛ ከተማ ድሬዳዋ ናት። በአዲስ አበባና
በድሬዳዋ ከተማ መካከል ያለውን ልዩነት በ12 እጅ
የሚበልጥ በመሆኑ በኢትዮጵያ ከተሞች መካከል
ያለው ልዩነት እጅግ የጎላ መሆኑን መረዳት እንችላለን
ይላል መግለጫው። ዞሮ ዞሮ ኢትዮጵያ ያላት ከተማ
አንድ እሱም ቢሆን አዲስ አበባ ብቻ ነው የሚሉ አሉ።
እሷም ብትሆን በቂ መብራትና ውሃ ገና አላገኘችም።
የአዲስ አበባ ቁጥር ግን ካለበት ሳይነቃነቅ 3ሚሊዮን
እንደተባለ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው? በዚህ
ስሌትስ እንዴት አድርጎ ነው የዛሬ አስር ዓመት 12

396 ከመቶ ?
መንግሥት ለራሱ አጨበጨበ

198 ሺ 667 ዜጎቹን ኤክስፖርት አድርጓል!
ባለፈው ዓመት፣ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2005 የበጀት ዓመት፣ “40,000
ዜጎችን በውጭ አገር ሥራ ለማሠማራት አቅዶ ለ198 ሺ 667 (10 ሺ736
ወንዶች እና 187ሺ 931 ሴቶች) አገልግሎት በመስጠት ከእቅድ በላይ 396
በመቶ አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡” ሲል የመንግሥት የአምስት ዓመት የእቅድና
ትራንስፎሜሽን አፈጻጸም ሪፖርት አመልክቷል። “አፈጻጸሙ ከባለፈውም
ዓመት ጋር ሲነጻጸር እጅግ በጣም ከፍ ያለ” መሆኑን ገልጾ “በ2007
በ2013/14 የበጀት ዓመት እንደሚደረስበት የተጣለው ግብ ሙሉ በሙሉ
ተደርሶበታል፡፡” ብሏል።

መንግሥት ይህን ይበል እንጂ ሰሞኑን ከሳዑዲ አረቢያ ብቻ ከ100ሺ በላይ
የሚሆኑ ተመላሽ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ማጓጓዙን እየገለጸ ነው።
እንኳንስ የዜጎቹ መብትና ደህንነት ሊከበር በተቃራኒው ከፍተኛ ቁጣን
የቀሰቀሰውና አሳዛኝ ግፍ የተፈጸመባቸው ዜጎችን ሲያጓጉዝ ተገኝቷል።
የስደት ተመላሾቹንም መልሶ በማጓጓዙ ከፍተኛ አድናቆት እንዲሰጠው
የሚጠባበቀው መንግሥት ይህንንም ከእቅድ በላይ ማከናወኑን ገልጿል።
10ሺ ሰዎችን ለመመለስ አቅዶ 10 እጥፍ የሚደርሱትን ከ100ሺ በላይ
ኢትዮጵያውያንን መልሶ ለማጓጓዝ በመቻሉ ተኩራርቷል።

በውጭ ሃገር ለሥራ የሚሠማሩ ዜጎች፣ መብትና ደህንነትን ለማስጠበቅ፣
እንዲሁም ህገ ወጥ የሠዎች ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል፣ አንድ
ብሄራዊ ኮሚቴ መቋቁሙን ሪፖርቱ አስታውሷል። በተለይ የሰዎች ህገ
ወጥ ዝውውርን በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንዲቻል በውጭ አገር
ለሥራ የሚሠማሩ ኢትዮጵያውያንን መብት ደህንነትና ክብር ለማስጠበቅ
ከፌዴራል በተጨማሪ በየክልሉ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ ማድረግ ናቸው፡፡

የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀን ወደ 800 የሚደርሱ ወደ
አረብ አገራት ተጓዥ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ፈቃድ በመስጠት ያስተናግድ
እንደነበረ መግለጹ ይታወሳል። የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ
ሸለመ “ሠራተኞችን ወደ ውጭ በሕጋዊ መንገድ ከሚልኩ 178 ያህል
ኤጀንሲዎች ጋር በጋራ እንደሚሠሩና ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኩዌትና ዱባይ

ከገጽ 2 ስብሐት
አቶ ስብሐት- እኔ ችግር ካለኝ ከሷ
ጋር ነው የምነጋገረው እንጂ...
ዘኢትዮጵያ -ግንኙነትዎ ጤናማ
ነው?
አቶ ስብሐት- ኸ?
ዘኢትዮጵያ
ግንኙነትዎ!

-ጤናማ

ነው

አቶ ስብሐት- እንዴ አንድ ድርጅት
ውስጥ ነውኮ ያለነው። ይሄ
የሥራቤት ድርጅትኮ አይደለም።
አንድ ጊዜ ተጣልተህ በሀሳብ
ከተለያየህ
ትወያይበታለህ።
የሀሳብ ልዩነት ብዙ ሰዎች አለን።
እነሱም ከኔጋር አለ..ስለዚህ ይሄ
ፀጋችን ነው። ንቁ ኃይላችን እሱ
ነው። ይሄ ባይኖር ነው ይሄ
ስላለ ያለሞከራረፍ ውይይት
ስለሚደረግ ነው TPLF ሁለትም
ሶስትም ሆኖ የማያውቀው። በዚህ
በሀሳብ ልዩነት መወያየት የተቸገረ
ይባረራል። በአንጃ ጊዜም ያየነው
እሱ ነው። ረገጡ! ትልቁ ሪሶርስ
ትልቁ ሀብት የተለያዩ ሀሳቦችን
ማስተካከል ይሄ ነው አቅማችን።
ከመጀመሪያው ብረት አልነበረም።
ስለዚህ ይሄ የድርጅት አሠራርና
ከህዝብ ጋር ያለን ግንኙነት። That
was the መድረክ that was
the ጥይት በውስጣችን የነበረው
ዴምክራቲክ ሕይወት ነው ይሄ

የሚያደናቅፍ ይባረራል። እና እኔ
አሁን የጠየቅከው የሀሳብ ልዩነት
ይኖራል። ኤፈርት እንደዚህ ይሁን
ይሄ እንደዚህ ይሁን ያ ሀብታችን
በረዶ የገባበት አይደለም።
ትኩስ ነው። ሕይወት አለው።
ፖለቲካዊ ህይወት ሁልጊዜ ትኩስ
መሆን አለበት። ትኩስ ካልሆነ
ትበላሻለህ። ከውስጥም ከውጭም
ኮሚኒኬሽን መኖር አለበት ንፋስ።
እኔ አሁን ያልከው ያነሳኸው
አንተ.....
ዘኢትዮጵያ - አለመስማትዎ ግን
ይገርማል ምክንያቱም የእርስዎና
የወ/ሮ አዜብ የሚባለው ነገር
ደጋፊዎችም ሳይቀሩ ቀላል ነገር
አይመስለኝም።
ምክንያቱም
ለረጅም ጊዜ የነበረ ነገር ነው።
እንዲያውም ወደ ቡድናዊ ደረጃ
የአዜብ ቡድን የአቶ ስብሐት
ቡድን እየተባለ የሚጻፍ የሚነገር
በደጋፊው በተቃዋሚው ውስጥ
የሚሰማ ነገር ነው።
አቶ ስብሐት- ሊኖር ይችላል!
ዘኢትዮጵያ - እና አለመስማትዎ
ገርሞኝ ነው!
አቶ ስብሐት- የሚሰማው ነው
እንትኑ። ይሄ የሚሰማ ጅል መሆን
አለበት። የሀሳብ ልዩነት ይነሳል
ወይ አይነሳም ይነሳል? እሱ ነው

ህይወታችን ይነሳል። ሺ ጊዜ
ተገልጿል። የውስጥ ፖለቲካዊ
ሕይወት መኖር አለበት!
ዘኢትዮጵያ -የሀሳብ ልዩነት ሲነሳ
ያፋጫል ብዙ ጊዜ፣ አንዳንዴ
ከድርጅትዎ እስኪባረሩም ድረስ
ያስኬዳል፤ እስከምንድረስ ነው
የሄደው የርስዎ የሀሳብ ልዩነት?
አቶ ስብሐት- እስከ ተፋጭቶ
እስኪታረቅ ድረስ። እሱኮነው
መጨረሻው
ተፋጭቶ
አልተለያየንም።
ተፋጭቶን
እስኪያቀራርበን ሄደ።
ዘኢትዮጵያ - ይሄ ስጋት ነበረ?
እርስዎ የሰጉበት ጊዜ ነበረ
በድርጅቱ አካሄድ ላይ ድርጅቱ
ሳስቷል ድርጅቱ አደጋ ላይ
ወድቋል ያሉበት ጊዜ ነበር?
አቶ ስብሐት- ስላልወደቀ ብዬ
አላውቅም።
ዘኢትዮጵያ - ምልክቱንም
አላዩትም?! ችግር የደረሰበትን
ጊዜ? (አቶ ስብሐት ድርጅቱ አደጋ
ላይ ወድቋል እያሉ ከድርጅቱ
የተሰናበቱ ሰዎችን ሳይቀር እየዞሩ
ያነጋግሩ ለማግባባት ይጥሩ
እንደነበር ሲነገር የኖረ ነው።)
አቶ ስብሐት- አንዳንድ ድክመቶች
ነበሩ። እሱ አሁን ወደ ገጽ 4

ሚሊዮን የሚደርሰው? ቁጥር ትክክል ካልሆነስ የአዲስ
አበባ ቁጥር ሁልጊዜ አንሶ እንዲነገር የሚፈለገው
ለምንድነው? እነዚህ ጥያቄዎች ጉዳዬ የተባሉ
አይመስልም። አሁንም ከሱ ከቁጥሩ ይልቅ ስለችግሩና
አደጋው ማውራቱ የቀለለ መስሏል። ብዛቱ አስከትሏል
የተባለው ችግር እየተወራ የብዛቱ መጠን የሚደበቀው
ለምንድነው? የማ ዕከላዊ ስታትስቲክስ ስለችግሩ
ሲወራ የሚከተለውን ብሏል፦
“ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየውና ከገጠር ወደ ከተማ
የሚደረገው ከፍተኛ የህዝብ ፍልሰት የከተማው
ኢኮኖሚ ያለውን ነዋሪ መሸከም በማይችልበት ሁኔታ
ላይ እያለ የተከሰተ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ባለው
ውስን ቁሳዊና ተቋማዊ አቅም ዘላቂ ልማት ለማምጣት
ተቸግሯል፡፡ በመሆኑም በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ
የመጣውን የከተማ ህዝብ ዕለታዊ ፍላጎት ለማሟላት
አዳጋች ሆኗል፡፡ ከዚህም የተነሳ የአዲስ አበባ ከተማ፣
ድህነትና ስራ አጥነት የተንሰራፋባት፣ የተዳከመ
የመሰረተ ልማት አውታር የሚገኝባት፣ የተጨናነቀ
የመኖሪያ አካባቢና ከደረጃ በታች የሆኑ ግንባታዎች
የተሞላች፣ ቀላል የማይባል ቁጥር የያዘ ነዋሪ መደበኛ
ባልሆነ የስራ መስክ ተሰማርቶ የሚገኝባት፣ የጎዳና
ተዳዳሪነት፣ ዝሙት አዳሪነት፣ ልመናና ወንጀለኛነት፣
የትራፊክ አደጋ፣ የንብረት ቃጠሎና ውድመት፣
ሕገወጥ ግንባታ ወዘተ የተንሰራፋባት መሆኗ ተጠቃሽ
ነው፡፡”
በአንድ በኩል ስለ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እየተወራ
በሌላ በኩል በአሃዝ ሳይሆን በአይነት ስለሚገለጽ
እንደዚህ ያለ ችግር የማውራት ፖለቲካ ግልጽ
አይደለም። የኢኮኖሚ እድገት ሲወራ ለእድገቱ
አስተዋጽኦ ያለውን የአምራች ህዝብ ቁጥር መጨመር
ለመሸሸግ ተፈልጎ ከሆነ ኢኮኖሚስቶች እዚህ ላይ
ቢያጫውቱን ከተሳካላቸውም ቢያስጠነቅቁን ጥሩ
ነው። 10 ዓመት ቅርብ ሲሆን የተባለው 12 ሚሊዮን
ደግሞ ብዙ ነው። ከአዲስ አበባ ህዝብ መውለድ
በሚችል የዕድሜ ክልል የሚገኘው 64 ከመቶ በላይ
ነው መባሉ ከግምት ሊገባ የሚገባው ነው። የወንድና
የሴቱም ቁጥር የሚለያይ ሲሆን የሴቶች ቁጥር
ከወንዶች ቁጥር ጋር ሲወዳደር በ16 በመቶ ብልጫ
አለው፡፡ 84 ወንዶች ለ100 ሴቶች ይደርሳሉ ማለት
ነው። ብዙ ወላድ አለ!

በሕጋዊ መንገድ ሠራተኞችን እንደሚልኩ” መናገራቸው በወቅቱ ተዘግቧል፡
፡ እንዲያውም የተጓዡ መጠን እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ መንግሥት ቶሎ ቶሎ
መላክ እንዲችል፣ “ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ለችግሩ መፍትሔ ለማግኘት
ቀደም ሲል ወደ ሌላ ቦታ ተዘዋውረው የነበሩ ሠራተኞቹን ሳይቀር በመመለስ
ላይ ይገኛል፡፡ በምሳ ሰዓት፣ ቅዳሜና እሑድ ሳይቀር ሠራተኞች በእረፍት
ቀናቸው እንዲገቡ እያደረጉ መሆናቸውን” ባለሥልጣኑ አስረድተዋል።
ስለዚህ መንግሥት ከኤጄንሲዎች (ደላሎች) ጋር ተባብሮ ለሥራ ወደ አረብ
አገራት የሚልካቸውን ዜጎቹን ሲልክም ሆነ ሲመልስ በኩራትና በትጋት
መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።

ባለፈው ዓመት ብቻ 30ሺ 269 የውጭ
ዜጎች ኢትዮጵያ ገብተው እየሠሩ ነው
በተያያዘ ዘገባ በ2012/2013 በጀት ዓመት መንግሥት ለ23,000 የውጭ አገር
ዜጎች የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት አቅዶ በድምሩ
ለ30,269 የውጭ አገር ዜጎች የሥራ ፈቃድ የመስጠት አገልግሎት ማከናወኑን
ገልጿል፡፡ አፈጻጸሙ ከዕቅዱ በላይ ሊሆን የቻለው በአገሪቱ በተፈጠረው
ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ እና እያደገ በመጣው የመሠረተ ልማት ግንባታ
ምክንያት ለሥራ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የውጭ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ
በመምጣቱ ነው ብሏል።

የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ!
የሠራዊቱን ጡንቻ የሚያፈረጥሙ ሕጎች እየወጡ ልዩ ልዩ ሹመቶች እየተሰጡ ነው። በዚህ መሠረት የጄኔራል
መኮንኖች ሹመትና በመከላከያ ሠራዊቱ አመራሮች ላይ የኃላፊነት ሽግሽግ ተካሄዷል፡፡ የሰሜን ዕዝ ዋና አዛዥ
የነበሩት ሌተና ጄኔራል ሰአረ መኮንን በተሻለ ኃላፊነት ወደ ማዕከል እንዲመለሱ መደረጉ ታውቋል፡፡ በምትካቸው
ሜጀር ጄኔራል ዮሐንስ ወልደ ጊዮርጊስ ተሹመዋል፡፡ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ በነበሩት ሜጀር ጄኔራል ሞላ ኃይለ
ማርያም ምትክ ሜጀር ጄኔራል አደም መሐመድ መተካታቸው ተገልጸዋል፡፡ ከአየር ኃይል አዛዥነታቸው የተነሱት
ሜጀር ጄኔራል ሞላ እንደ ሌተና ጄኔራል ሰአረ ወደ ማዕከል ለከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት መሾማቸው ተዘግቧል፡
፡ ሹመቱን ተክትሎ የአገር መከላከያ ሠራዊት የሚተዳደርባቸውን የተለያዩ አዋጆች በአንድ ያጠቃለለና የተለያዩ
ማሻሻያዎችን ያካተተ አዋጅ መዘጋጀቱም ተገልጿል።
( ለአብነት ያህል ጠ/ሚኒስትሩን በማስፈቀድ ከሚል ለበጣ ጋር የሚከተሉት መብቶች ለመከላከያ ተሰጥተዋል)
•	

ከፌዴራል መንግሥት በየዓመቱ ከሚያገኘው በጀት በተጨማሪ፣ ከሌሎች የገቢ ምንጮች እንዲጠቀም
በሕግ ተፈቅዶለታል።

•	

በተቆጣጣሪ ባለሥልጣንነት የሚመራቸው የልማት ድርጅቶች በየዓመቱ ከሚያገኙት ትርፍ ላይ ድርሻ
እንዲኖረው፣ ሕጋዊ ፈቃድ አግኝቷል፡

•	

በተለያዩ አገሮች የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ሠራዊቱን በማሰማራት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
የሚያገኘውን ክፍያ (በውጭ ምንዛሪ) መጠቀም ይችላል።

መከላከያ ሚኒስቴር ካሉት አትራፊ የልማት ድርጅቶች መካከል
•	

የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን

•	

ግዙፉ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣

•	

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝና

•	

የመከላከያ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ኢንተርፕራይዝ ይኙበታል።

ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ከሁለት ዓመት በፊት በአሥር ቢሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ግዙፉ የብረታ ብረትና
ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በተቋቋመ በሦስተኛ ዓመቱ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ እያንቀሳቀሰ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ
በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዓመታዊ ትርፍም እያገኘ ነው፡፡ መንግሥት በአጠቃላይ ለመከላከያ የሚፈቅድለት በጀት
(ለምሳሌ በዚህ ዓመት) 7.5 ቢሊዮን ብር ቢሆንም ከበርቴው መከላከያ ግን ካሉት ድርጅቶች መካከል በአንዷ ብቻ
ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ ያንቀሳቀሳል።
ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com

ፍሬነገር

“አለ”-የኢትዮጵያ ዎልማርት!
ሁሉንም ነገር እንሸጣለን ሁሉንም ነገር እንገዛለን

መንግሥት ሌላ
አዲስ የንግድ
ድርጅት አቋቋመ

የኑሮ ውድነቱ እንዴት ተቻለ?
መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ!?
“ኑሮ ተወዷል” ያልተባለበትን
ቀን ለማስታወስ ከማይቻልበት
ደረጃ ተደርሷል። ሰው ግን እየኖረ
ነው! ምንድነው ተአምሩ? ሰው
እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ማወቁ
ይቸግር ይሆናል። መንግሥት
የሚያደርገውን ግን መመልከት
ይቻላል። ለሠራተኞች ደመወዝ
ጨምሯል፣ በሸቀጦች ላይ ጊዜያዊ
ተመን አውጥቷል። ሕገ - ወጥ
ነጋዴዎች ያላቸውን የመቅጣት
እርምጃ ወስዷል። ያለቅጥ
የሚሰጠውን የባንክ ብድር
በመግታት ግሽበቱን ለመቆጣጠር
ሞክሯል። ምንዛሪ በመሸጥ ከፍተኛ
የሆነ የዶላር ክምችት ፈጥሯል፡
፡ ከእነዚህ ሁሉ የላቀው ግን የኑሮ
ዋልታ የሆነውን የእህል አስቤዛ
ገዝቶ መደጎም ነው።
መንግሥት ተጠሪነቱ ለንግድ
ሚኒስቴር የሆነ የኢትዮጵያ እህል
ንግድ ድርጅት የሚባል ተቋም
አለው። ሥራው ከውጭም ሆነ
ከአገር ውስጥ እህል እየሸመተ
በርካሽ ዋጋ ለገበያ ማቅረብ ነው።
እንደ መንግሥት እምነት ይህ
ድርጅቱ እስካለ እህል እጥረት
አይኖርም ፤ ዋጋም ርቆ አይሄድም።
ለምሳሌ ባለፉት ሁለት ዓመታት
በኩንታል እስከ 800 ብር ደርሶ
የነበረውን የስንዴ ዋጋ ወደ 580
ብር ጎትቶ ጥሎታል። ለእንዲህ
ያለው ጨዋታ እስካሁን ከ18
ሚሊዮን ኩንታል በላይ ስንዴ
ከውጭ ገዝቶ አስገብቷል። ለምሳሌ
አምና በ2005 ዓመተ ምህረት
ብቻ 5.6 ቢሊዮን ብር ወጪ
አድርጎ ከ5 ሚሊዮን ኩንታል
በላይ እሕል በመግዛት ገበያውን
ዝም አሰኝቶታል። ለዳቦ ጋጋሪዎች
የሚሆን ዱቄት ለሚያመርቱ
ፋብሪካዎች 6 ሚሊዮን ኩንታል
ስንዴ ገዝቶ አድሏል። ከገበሬዎች

ላይ ከ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ
እህል ገዝቷል። ድርጅቱ ዘንድሮ
ከሀገር ውስጥና ከውጭ እህሉን
ለመግዛት 4 ቢሊዮን ብር መድቦ
እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት
በመላ አገሪቱ 10 ቅርንጫፎች እና
ከ70 የማያንሱ የግዥ እና ሽያጭ
ጣቢያዎች አሉት።

እህል ገዝቶ (ወይም ከጎተራው
አውጥቶ) ገበያው ላይ ለመርጨት
አስቧል። ይህ መንግሥት በገበያው
ላይ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት
ያሳያል ብለው የሚተቹት አሉ።
ከዚያም አልፈው እንዲያውም
ለዋጋ ውድነቱ የመንግሥት ጣልቃ
ገብነት ተጠያቂ ነው ብለው
የሚከሱትም አሉ። ምክንያቱም
መንግሥት
ለበላተኞችም፣
ለአከፋፋዮችም፣ ለእርዳታ ሰጪ
ድርጅቶች ሳይቀር እህል እየገዛ
ስለሚሸጥ ብዙ እህል ያስፈልገዋል።
ኪሳራም ስለማይኖርበት ከገበሬው
በተጠየቀው ዋጋ ተሻምቶ ይገዛል።

ከዚያ የሚያገኘውን ዶላር መልሶ
እህል ይገዛበታል፣ በገዛውም
እህል ገበያውን ያረጋገበታል።
“ኢትዮጵያ በምግብ እህል ራሷን
ትችላለች” ሲባል አምርታ ሳይሆን
ገዝታ በመመገብ ነው መባሉም
ለዚህ ነው። ገበያው ሰማይ
ቢደርስ ግሽበቱ (ኢንፍሌሽኑ)
ቢፈላ፣ መንግሥት የተወደደውን
እያስረከሰ፣ የረከሰውን እያስወደደ
ሚዛኑን እያጫወተ ይጠብቃል።
ከውጭም ሆነ ከውስጥ፣ ጨው፣
ስንዴ፣ ዘይትና ቅመማቅመሙን
ሲገዛ በአንድ ስሙ ወጥ ሠርቶ
ማቅረብ ቀርቶታል።

በዚህ ዓመት ካለው እቅዱ
መካከልም 100ሺ ኩንታል ጤፍ፣ 4
ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የስንዴና
የቦቆሎ ምርት የመሳሰሉትን 7
ሚሊዮን ኩንታል ከገበሬው
በመግዛት
ገበያውን
ለማጥለቅለቅ እቅድ ይዟል።
ችግር ሲፈጠር ቶሎ ከኢትዮጵያ ትልቁን የእርሻ መሬት የገዙት ህንዶች ናቸው።
ገዝታ የምታስመጣው
ለመድረስ በሚል በአሁኑ ኢትዮጵያ ደግሞ እህል/ስንዴ
ወቅት 8 ሚሊዮን ኩንታል ከህንድ ነው። በዚህ አመት መስከረም ወር ብቻ ከገዛችው 4
እሕል የማከማቸት አቅም
ፈጥሯል፡፡ 40 ሚሊዮን ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታሉ
ህዝብ ቢራብ ለ6ወር የተገዛው ከህንድ ነው። መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ!
መቀለብ እችላለሁ ባይ
ሆኗል። ለዚህም አሁን
በመጠባበቂያ ክምችት ያለውን
እንዲህም ሆኖ ኑሮ ውድነቱ
በጅምላም ቸርቻሪም አስመጪም
የ465 ሺሕ ሜትሪክ ቶን የእህል
ቀጥሏል።
እስከመቼ?
ላኪም ስለሆነ በብዛት የተሳተፈበት
ክምችት፣ ወደ ሦስት ሚሊዮን
አይታወቅም። ቢሆንም ቢሆንም
ንግድ ሀብታም አድርጎታል። ከአገር
ሜትሪክ ቶን በማሳደግ፣ 40
ዛሬ...ሰው በልቶ ያድራል! ገዝቶም
ውስጥ አልፎ ኤክስፖርት ለማድረግ
ሚሊዮን ሕዝብ ለስድስት ወር
ሆነ ተገዝቶ ወይም ፖለቲካው
ቡናና የቅባት እህሎችንም መሸጥ
መመገብ የሚያስችሉ የእህል
ሌላው ነገር ሆኖ ማለት ነው!
መጀመሩም ለዚህ ነው። ቡና እየላከ
ማከማቻ ጎተራዎችን እየገነባሁ ነው
በነገራችን ላይ ከኢትዮጵያ ትልቁን
ስንዴ ለማስመጣት ተነስቷል።
ብሏል። በቂ መብራት ሳይኖረው
የእርሻ መሬት የገዙት ህንዶች
ለጎረቤት አገሮች ኤሌክትሪክ
መንግሥት በእህል ንግድ ድርጅት
ናቸው። ኢትዮጵያ ደግሞ እህል/
ኃይል እሸጣለሁ እንደሚለው
አማካይነት፣ እንኳን አገር ውስጥ
ስንዴ ገዝታ የምታስመጣው ከህንድ
እህልም ኤክስፖርት አደርጋለሁ
ያለውን
ፍጆታ
ኢትዮጵያ
ነው። በዚህ አመት መስከረም ወር
ብሎ ተነስቷል። በነዚህ ምክንያቶች
ወደ
ውጭ
በምትልካቸው
ብቻ ከገዛችው 4 ሚሊየን ኩንታል
መንግሥት ወደ ገበያ መርጨት
የኤክስፖርት ምርቶች ላይ ሳይቀር
ስንዴ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን
ሳይሆን ከገበያም ይሰበስባል
እጁን አስገብቷል። በዚህ ዓመት
ኩንታሉ የተገዛው ከህንድ ነው።
ማለት ነው። ገበያው ላይ እጥረት
56 ሺ ኩንታል የቡና ምርት
መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ!
መፈጠሩም ለዚህ ይመስላል። ራሱ
ከገበሬው በመግዛት ወደ ውጭ
ያቆሰለውን ገበያ ራሱ ያክመዋል።
አገር ልኳል። 195ሺ ኩንታል
የጥራጥሬና
የቅባት
እሕል
በዚህ ዓመት 6.5 ሚሊዮን ኩንታል
ምርቶችን ኤክስፖርት አድርጓል።

የዲሲ መንግሥት ባለታክሲዎችን
እያማረረ ነው
የታክሲ ሥራ እንዴት ነው?
ታክሲ ጥሩ ሥራ ነው። ገቢውም የተረጋጋ ኑሮ
ለመኖር ያስችላል። በብዙ አንጻር ሕብረተሰባችንን
የሚደግፉት ባለታክሲዎች ናቸው። ታክሲ ሥራ
ጊዜ እንደ አግባቡ ለመጠቀም ያስችላል። ልጅ
ማሳደጊያ ጊዜ ይሰጣል። የታክሲ ባለቤትነት
ማለት የንብረት ባለቤትነት ማለት አይደለም
የገዛ ሕይወት ባለቤትነት ማለት ነው። በህይወት
ውስጥ ትልቁ ሀብት ጊዜ ነው። በራስ ጊዜ
መወሰንን የመሰለ ባለቤትነት የለም። አሁን ግን
ያንን ባለቤትነቱን እያሳጡት ነው። “በተዘዋዋሪ
ቅጥረኛ የሚያደርገውን ሕጎች አመጡ። ማሽኑ
ታክሲው ላይ ይገጠማል። ያ ማሽን በምን ሰዓት
የት እንደነበርክ ምን ያህል እንደሠራህ ይናገራል።
ምናልባት በየዋህነት “ታዲያ ምን አለበት?”
ተብሎ የሚታለፍ ሊመስል ይችላል። ግን
ይህ ያስፈለገው ለምንድነው? ሄዶ ሄዶስ
ምን ሊያስከትል ይችላል? የሚለው መታየት
ይኖርበታል። ድሮ ስምንት ሰዓት ብቻ ይሠራ
የነበረ ሰው አሁን 10 ሰዓት መሥራት ያስፈልገው
ይሆናል። ድሮ 12 ከሆነ አሁን 14 ሰዓት ይፈጃል።
5ቀን ብቻ የሚሠራው አሁን ሳምንቱን ሙሉ
ሠርቶ ላይበቃው ይችላል። ይህ በቤተሰብ ላይ
ለሕብረተሰባችን በሚደረግ የበጎ አድራጎት ሥራ
ላይ ችግር ያመጣል። ገቢም ላይ የሚያሳድረው
ጫና ይኖራል። የዲሲ መንግሥት ሕጎችን
የሚያውቁው አንድ ታክሲ አሸከርካሪ 40 ሰዓትና
አምስት ቀን ሰርቶ ከ25-30ሺ ዶላር በዓመት
መሥራቱን ነው። ከዚያ በላይ የሚሠራ የበለጠ
ሊያገኝ ይችላል። አሁን እንኳን ከዚያ የበለጠ
ሊሠራ ለአብዛኞቹ ያለውንም ይዞ መቀጠል
አሳሳቢ እየሆነ ይመስላል?

ለውጡ ያስፈለገው ለምንድነው?
ነገሩ ሲጀመር እንዲህ ነው። በ2011
“Modernization of taxi cab Industry “
ተባለ። የታክሲ አገልግሎትን ዘመናዊ ለማድረግ
መሆኑ ነው። ለዚህ ሲባል አንዳንድ ደንቦች
ወጡ። አንደኛ ክሬዲት ካርድ ማሽን መግጠም።
ሁለተኛ ቀለም የታክሲ ቀለም አንድ ዓይነት
እንዲሆን (ታክሲዎች አንድ ዓይነት እንዲቀቡ
ማድረግ) ። ሶስተኛ ከታክሲው አናት ላይ
የሚያበራ ምልክት (ዶም ላይት) እንዲገጠም።
አምስተኛ ነዳጅ ቁጠባ ወይም አየር ብክለት
መቋቋሚያ እንዲሆን በኤልክትሪክ የሚሠሩ
(ሃይብሪድ) መኪኖች... እንዲሆኑ ተባለ። ደንብ
በደንብ ላይ እየተነባበረ መጣ።
ችግሩ ደንቡ መከበሩ አይደለም። ችግሩ የታክሲ
አሰራር መሻሻሉ ሳይሆን ወጪው በሙሉ
በታክሲ ነጂ ላይ እንዲጫን መሆን ብቻ ሳይሆን
ታክሲ ነጂው በጥድፊያን በውድ እንዲገዛ

4

መደረጉ ነው ::ከዚህም በተጨማሪ ታክሲ ነጂው
በ እየአንዳንዱ መንገደኛ 0,25 ሳንቲ እንዲከፍል
ሲደረግ የሰራበትንም ገንዘብ ከ ጵጽጵ ዎች
ተሰልፎ እንዲቀበል ተደርጓል:: ግን ክሪዴት
ካርድ ማሽን ሲገጠም ማሽንኑን የሚገጥመው
ማነው? ስንት ያስከፍላል? የባለታክሲው
መብት እዚህ ላይ ምንድነው የሚለው ነው።
ኩባንያዎችን ለመጥቀም ሲባል የማሽኑ ዋጋ
ከተቆለለ ማን ይከፍላል? ለምንድነው ገበያው
መወሰን ሲችል ከዚህ ኩባንያ ብቻ ግዙ
የሚባለው? እዚህ ላይ ያልተቃወሙት አሠራር
በጊዜ ሂደት ባለታክሲዎችን በወጪ እያደቀቀ
ከገቢያ ያስወጣቸዋል። ነገ ይህን ዓይነት መኪና
ብቻ ግዙ ፤ ስትግዙ ደግሞ ከዚህ ኩባንያ ብቻ
ነው የምገዙት ማለትን ያመጣል። ያን የቻለ ሲገዛ
ያልቻለ ከገበያ ይወጣል። ምክንያቱም ይህንን
ችግር የዲሲ መንግሥት ያውቀዋል። በማወቁም
ነው የክሬዲት ካርድ ማሽኑ ማስገጠሚያ ወጪ
ሊበዛ ስለሚችል መጀመሪያ እኔ እከፍላለሁ ብሎ
ነበር። ኋላ ደግሞ የለም እንዲያውም 35 ሚሊዮን
ዶላር በጀት ልመድብና ሌላውን ባለታክሲዎች
ይክፈሉ ተባለ። ባለታክሲዎች ከከፈሉ ደግሞ
ምርጫ ይሰጣቸው ተባለ። መምረጥ የሚችሉት
ግን ከነዚህ 8 ድርጅቶች ብቻ ነው ማሽኑን ግን
በ100 ዶላር ይግዙት በማለት አስገደዱ። አንድ ሺ
ምርጫ እያለን 8 ብቻ ለምን ይሆናል? ሌላ ስቴት
ግን ይህ የለም። ለምሳሌ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ
ያሉት ባለታክሲዎች ራሳቸው ሄደው መርጠው
እንዲገዙ ነው ምርጫው የተሰጣቸው።

ዲሲ ግን እንዲሠሩ ተፈቅዶላቸዋል። ይህ ሙስና
ሊኖርበትም ቢችል ግልጽ አድልዎ ነው። ይህን
በሚመለከት ክስ ተመስርቶ ጉዳዩ ጃንዋሪ 20
ይሰማል።

የተፈራው ደረሰ?!ስሕት እንደ
ትክክል ሲቆጠር ::

ለዚሁ ሁሉ ችግሩ ሰዎች አይጠይቁም።
አንብበው ከመረዳት ይልቅ በሰሙት የመነዳት
ነገር አለ። መረጃውንም በጽሑፍ የሚያቀብል
ወገን የለም። ሁሉም ነገር የሚንቀሳቀሰው በወሬና
በስማበለው ነው። የሚያወሩትም ሰዎች ስለጉዳዩ
በጥልቀት የሚያውቁ አይደሉም። በጉዳዩ የተካኑ
ጉዳዩን ሥራዬ ብለው የያዙት አዋቂዎችን
ከመስማት ሁሉም አዋቂ እየሆነ ነገሮችን
ይምታታሉ። እንደ ፖለቲካው ሌላ የማያስፈልግ
መልክ እየያዙ ለንትርክ ለሐሜትና ለጥርጣሬ
በር ይከፍታሉ። “እንድ ሰው ዛሬ ተነስቶ
እንደዚህ ሊደረግ ነው ሰው ሁሉ መኪናውን
ቶሎ ቢሸጥ ያዋጣውል ብዬ ብናገር የሚያምነኝ
ብዙ ሰው አላጣም። እንዴት? ለምን? ማን
ያለው ብሎ መመርመር የሚወድ የለም። ይህም
የራሱ አስተዋጽኦ አለው።” ብለዋል አቶ ዓለሜ።

የተገጠሙ ማሽኖች ቶሎ ቶሎ መበላሸት
ጀምሩ። የተበለሸውን ማሽን ለማሠራት ለዚህ
ብቻ የተመደቡ ጋራዦች ከአቅማቸው በላይ
እየሆነ ባለታክሲዎች መኪኖቻቸው ወስደው
ጋራዥ ማቆም ጀምረዋል። አንዳንዴ ከ4-5 ሰዓት
ታጠፋለህ። ጋራዦቹ በቂ እውቀት የሰለጠነ በቂ
የሰው ኃይል የላቸውም። በዚያ ላይ ወጪው
ቀላል አይደለም። በየእያንዳንዱ ጉዞ (ትሪፕ)
25 ሳንቲም ክፍሉ ማለቱም ሌላው መነጋገሪያ
ነው። በዲሲ ታክሲ ኮሚሽነሩ አማካይነት
ባለታክሲዎች ላይ ጦርነት የታወጀ ይመስል
ያለቅጥ የተንዛዛው ቁጥጥርም አሳሳቢ ነገር
ነው። ለምሳሌ አንድ ዓይነት ቀለም መቀባት
ላይ ያለው አሠራር የሚገርም ነው። እኛ ላይ
ጠበቅ ያለው ቁጥጥር ሌሎች ላይ አይሠራም።
ለምሳሌ UBER X የተባለው የታክሲ ኩባንያ
ያለ ቁጥጥር (without Regulations) እንዲሠራ
ተፈቅዶለታል። እነሱ የተደራጀ አቅም ስላላቸው
ቀለም የመቀባት ግዴታ የለባቸውም። ሌሎች
ስቴቶች ቨርጂኒያም ሆነ ሜሪላንድ የተከለከሉ

ከዚህ ለመውጣት ኢትዮጵያዊው ለመብቱ
መታገል አለበት። ያ ደግሞ የመደራጀትን
አቅም ይጠይቃል። ለዚህም ሲባል በርካቶች
የአሜሪካ ሠራተኛ ማህበር (Teamsters ) ውስጥ
ገብተዋል። እዚያ መግባቱ ብቻውን ግን በቂ
አይደለም። ተገቢውን ወርሃዊ ክፍያ መክፈል
ይገባል። ያ ባለመሆኑ ከድርጅቱ የተፈለገውን
እርዳታና አቅም ማግኝት አልተቻለም።
በዋሽንግተን ዲሲ ፖለቲካው ውስጥም ገብቶ
ተጽእኖ ለማሳረፍ ትልቁ ችግር አብዛኛው ታክሲ
አሽከርካሪ የሚኖረው ዲሲ ሳይሆን ሜሪላንድና
ቨርጂኒያ ውስጥ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ
ዲሲም ውስጥ ቢሆን ኢትዮጵያውያን ያላቸው
ጉልበት ከሚያውቁት በላይ መሆኑን የሚገልጹ
አሉ።
ምንም እንኳን ቲምስተር ለመርዳት አቅሙ ኖሮት
ፈቃደኛ ቢሆንም ጉዳዩን ታክሲ የሚነዳ ብቻ
የሚያውቀው በመሆኑ ቲምስተርን መገፋፋት
ተገቢ ነው::በሜሪላንድ እና ቨርጂኒያ የአሉት
ሴናተሮች ኮንግረስ ተመራጫጮች ጉዳያችንን
እንዲያዩ ማደረግ ሲገባቸው ቲምስተር እስከ
አሁን ለምን ይህንን እንዳላደረገ መጠየቅ ተገቢ
ነው::

“አዋቂዎችን የማፍራት እነሱን የመከተል ልምድ
ሊኖረን ይገባል። መኪናችን ሲበላሽ መካኒክ ጋ
ወስደን እናሰራለን መብታችን ሲበላሽ ግን እኛ
አዋቂዎች የምንሆነው ለምንድነው? መብታችንን
ይበልጥ ማስከበር የምንችለው ጉዳዩን ወደ ሥራዬ
ብለው ወደ ተከታተሉትና ወደ
ወደ ገጽ 10
ሚያዉቁት ሰዎች ስንወስድ ነው።

በንግድ
ሚኒስቴር
ሼር
እንዲተዳደር
በመንግሥት
የተቋቋመው “አለ” የተባለው
የኢትዮጵያ ጅምላ ንግድ ድርጅት፣
አትራፊ ሆኖ በግል ኩባንያነት
ይተዳደራል። በስም ጅምላ ይሁን
እንጂ በቸርቻሪ ሱፐር ማርኬት
ገበያነትም ይንቀሳቀሳል። የአንድ
ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል
አለው። ሁሉንም የምርት ዓይነቶች
ገበያው ውስጥ ለማገበያየት የተነሳ
ነው። የጅምላ ንግድ ድርጅቱ
“አለ” ሠራተኞቹን በተለይም
ማኔጅመነቱን ከአገር ውስጥና
ከውጭ እየቀጠረ ነው።
ኢትዮጵያው ውስጥ እንደ ዎል
ማርት ዓይነት የገበያ ድርሻ
ይኖረዋል ተብሏል። በዓለም
አቀፍ ደረጃ ካሉ የሸቀጥ
አቅራቢዎች ጋር እየተነጋገረ ነው።
ሸቀጦቹ ለሆቴሎች፣ ለግሮሰሪዎች፣
ለኪዮስኮች፣ ለባርና ሬስቶራንቶች
ከገጽ 3

ይከፋፈላሉ። ከምርቶቹ መካከል
የሸቀጣ ሸቀጥ፣ የተለያዩ መጠጦች፣
የታሸጉ ምግቦች፣ የውበትና የግል
ንጽህና መጠበቂያ፣ የጽህፈት
መሳሪያዎችና የሌሎች ምርቶች
ይገኙበታል። እነዚህን ሸቀጦችን
እያስመጡ የሚሸጡ ድርጅቶች
ከአሁን
በኋላ
መንግሥት
ከአቋቋመው የጅምላ መደብር
እንዲገዙ ይደረጋል። ተጠቃሚዎች
ደግሞ
ከድርጅቱ
ወይም
ከአከፋፋዮቹ ይገዛሉ። በአዲስ
አበባ ውስጥ የመጀመሪያዎቹ
ሦስት የጅምላ መሸጫ መደብሮች
በኤፕሪል 2014 ፣ በመርካቶ
በቃሊቲ እና መገናኛ አካባቢ
ይከፈታሉ።ከዚያም በሌሎች
26 ከተሞችም 37 አከፋፋይና
የችርቻሮ መደብሮችና ትላልቅ
መጋዘኖች
እንደሚኖሩት
ተነግሯል። እየተባባሰ የመጣውን
የዋጋ መናር ለመቆጣጠርና
ከንግዱ ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን
ገቢ ከፍ ለማድረግ ሌላ አማራጭ
ተደርጎ መወሰዱም ተገልጿል።
ከነጻ ገበያው ጋር ፍጹም
ተጻጻሪና የመንግሥትን ሁሉን
ነገር የመቆጣጠር ፍላጎት ተደርጎ
መታየቱም አልቀረም።

ስብሐት

ግንዛቤ አግኝቷል። (TPLF)
ህወሃት ሰው ወደደም አልወደደም
መለስ ከነበረበት በጣም የጠነከረ
ድርጅት ይሆናል። አሁን እንኳ
ከነጥንካሬው ነው ያለው።
የጥንካሬው ዲግሪ መለስ ከነበረበት
በላይ ጠንክሮ ይወጣል። ሰው
ይወደዋል ወይ አይወደውም
አይደለም። የትግራይ ህዝብ ግን
ወደዚህ ደረጃ ይደርሳል።

ሳቅ አቋረጣቸው አንድ ድርጅት
የበለጠ ከሆነ ያ...

ዘኢትዮጵያ - የመለስ ራዕይ ይባላል
አሁን ለምሳሌ ። ሁለት አየር ላይ
ያሉ ነገሮች አሉ። አንዱ ወገን
አቶ መለስ ህወሓትን ገድለውት
ነው የሄዱት። ይህንን አስተሳሰብ
እንዲያውም እነ አቦይ ስብሐት
የሚጋሩት ነው፣ የሚቆጩበት
ነው፣ የሚል አለ ። በሌላ በኩል
ደግሞ የለም መለስ ገድሎት
ሳይሆን እንዲያውም አጠናክሮት
ነው የሄደው የሚሉ ወገኖች አሉ
የእርስዎ አስተያየት ምንድነው?

ዘኢትዮጵያ - አቶ መለስ
አምባገነን ነበሩ እየተባለ የሚሰጥ
አስተያየትም ስላለ ነው። ሥልጣን
በተለይ ከፍፍሉ ወይም እነዚያ
ሰዎች ከተባረሩ በኋላ መለስ...

አቶ ስብሐት- እኔ አሁን እንደዚህ
እንትን ስለሆን አንድ ላይ ስለሌለን
አስቸጋሪ ሊሆን ነው........ አንድ
ድርጅት አንድነትንም ይሁን
አረናም ይሁን እንደ ድርጅትነቱ
ይወለዳል ይሞታል ይለወጣል
ይሻሻላል። TPLF ከመለስ በኋላ
የሚቀጥል አለው የሚቀጥሉ
ጸጋዎች አሉ የሚሻሻሉ አሉ፣
የሚለወጡ አሉ። ስለዚህ ይሄ
ኢተርናል ነው። ይሄ የሚሻሻል
አለ፣ የሚቀጥል አለ፣ የሚለወጥ
አለ። አሁን በፕሮግራም የሚለወጥ
ነገር የለም። ያው ካፒታሊዝም
ካፒታሊዝም ነው። ካፒታሊዝሙ
ደግሞ ደቨሎፕመንታል ነጻ አገራዊ
ኢኮኖሚ ነው። ስለዚህ መለስ
ድርጅቱን ገድሎት አልሄደም።
እንደማንኛውም ድርጅት አባይ
ስዬ ሄደ ትቶት የሚሄድ የሚሻሻል
ነው የሚለውጥ ነው የሚቀጥል
ነው ዳይናሚካሊ እንደሱ እያለ
ይሄዳል። እና መለስ ድርጅቱን
አልገደለውም።
በህይወቱ
ነው ያለው ግን ይጠነክራል።

አቶ ስብሐት- ሥራ ሁልጊዜ
ኮምፔሌክስ እየሆነ ይሄዳል
አይደለም? አሁን ማስፋቱ በጣም
አስፈላጊ ነው። It is very
important! ሁለት ተጠባባቂ
ጠቅላይ ሚኒስትሮች አደረገ።
ሁለት ነው ሶስት?

ዘኢትዮጵያ - ግን የሳቸው አመራር
ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/
ማርያም ወደ ስልጣን ሲመጡ
“አሁን የቡድን አመራር (ኮሌክቲቭ
ሊደርሺፕ) ነው ያለው” ብለው
ነበር። አሁን ነው ብለው ያሉት።
ከአቶ መለስ ሞት በኋላ። ምን
ማለት ነው ? ያ ቡድን አመራር
ማለት? አሁን የጋራ አመራር
አለ ብለው ያምናሉ? በፊትስ
አልነበረም ብለው ያምናሉ?
አቶ ስብሐት- እኔ አቶ ኃ/
ማርያም ይሄን ቢመልሰው
ነው
ጥሩ
የሚሆነው።
ዘኢትዮጵያ
ግን
ልክ

-

አባባሉ
አይደለም?

አቶ ስብሐት- የአቶ ኃ/ማርያም
አባባል ከየት እንደተነሳ ወደ
ግጭት መሄድ አልፈልግም።
ምን ማለቱ እንደሆነ። ድሮ የጋራ
አመራር አልነበረም ማለቱ ነው
ልል አልችልም። ነበረ ማለቱ ነው
ልልም አልችልም። ከኃይለማርያም
አልነሳም። ድርጅቱ ከነበረው
የጋር አመራር የበለጠ የጋራ
አመራር አግኝቷል አሁን።
ድሮም ባህርይው የጋራ ነው።
ዘኢትዮጵያ
የበለጠ

-

ለምንድነው
ያገኘው?

አቶ ስብሐት- ሳቅ...ሁል ጊዜ ምን
አልኩህ አንድ ድርጅት...አሁን

ዘኢትዮጵያ - ገባኝ ግን...
አቶ ስብሐት- አይደለም። የበለጠ
ካልኩህ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ
ነው። ድሮም የጋራ አመራር ነበር።
አሁን እሱ አሰፋው። ማስፋቱ
የጋራ አመራሩ ማስፋቱ ስለተገኘ
ነው። ማሻሻል..

አቶ ስብሐት- ይቺ ድገማት
አሁን ይቺ ድገማት? ድሮም የጋር
አመራር ነበረ። አሁን ደግሞ የጋራ
አመራሩን ማስፋት አስፈለገ።
ዘኢትዮጵያ - ለምን ማስፋት
አስፈለገ አሁን የጋራ አመራሩን?

ዘኢትዮጵያ - ሶስት ነው
አቶ ስብሐት- አራት ከፍተኛ
ባለሥጣኖች ደግሞ አድቫይዘርስ
ብሎ አስቀመጠ። በረከት አባይ..
ዘኢትዮጵያ - ካሱና ኩማ
አቶ ስብሐት- አዎ አስፈላጊ ሆኖ
አገኘዋ! ልሰራ ይሄ ያስፈልገኛል
አለ። ይሄ ትክክል ይመስለኛል።
ድሮም የጋራ አመራር ነበረ።
አሁንም ደግሞ ያ የጋራ አመራሩ
አሰፋው። ለምን ይሄ ነው
የሚቀለኝ በዚህ ነው የተሰጠኝን
ሥራ ልፈጽም የምችለው አለ።
ዘኢትዮጵያ - የመለስ ራዕይ
ይባላል፣ የኢህአዴግ ራዕይ፣
የመለስ ራዕይ ምን ማለት ነው?
መለስ የራሳቸው ራዕይ ነበራቸው?
በድርጅቱ ውስጥ? የመለስን
ራዕይ ለማስፈጸም ይላሉ ከኃ/
ማርያም ጀምሮ ሁሉም የድርጅቱ
አመራር አባላት እርስዎ ማለትዎን
አላስታውስም ግን ምንድነው
የሚመስልዎት?
አቶ ስብሐት- የኢህአዴግ ራዕይ
ነው። መለስ ይህንን ራዕይ
እውን እንዲያደርግ ወሳኝ ሚና
ተጫውቷል። ፋክቱን ነው
የምነግርህ ራዕዩ የኢህአዴግ ነው
በዚህ ራዕይ መለስ ወሳኝ ሚና
ተጫውቷል።
ዘኢትዮጵያ - የአቶ መለስ ጠንካራ
ጎኖች ብዙ ተብሎላቸዋል፣ ደካማ
ጎናቸው ምንድነው?
አቶ ስብሐት- ደካማ ጎኑ ብዙ
ጎልቶ የሚታይ (Noticable)
አይደለም። ጠንካራ ጎኑ የጎላ
(dominant) ነው።
ዘኢትዮጵያ - እርስዎ ምንም ቅሬት
አልነበረትዎም በድርጅቱ አካሄድ
ከውጭ ሆነው በሚያዩት?
አቶ ስብሐት- ብዙ የሀሳብ ልዩነት
ነበረ። በጣም! በጣም ብዙ የሀሳብ
ልዩነት ነበረ።
ዘኢትዮጵያ - ለምሳሌ ምንድነው
ከነበሩት የሀሳብ ልዩነቶች በጣም
ትልቁ ነው የሚሉት?
የጎላው ምንድነበረ? ወደ ገጽ 6
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014
Zethiopia Newspaper Jan 2014

More Related Content

Similar to Zethiopia Newspaper Jan 2014

Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...
Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...
Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...Ethio-Afric News en Views Media!!
 
Why does the Ethiopian government EPRDF shouts ? Ehadeg slemn ychohal
Why does the Ethiopian government EPRDF  shouts ?  Ehadeg slemn ychohalWhy does the Ethiopian government EPRDF  shouts ?  Ehadeg slemn ychohal
Why does the Ethiopian government EPRDF shouts ? Ehadeg slemn ychohalEthio-Afric News en Views Media!!
 
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articles
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articlesኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articles
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articlesMuhammad Shamsaddin Megalommatis
 
Yehaya amet debdabe/ A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...
Yehaya amet debdabe/   A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...Yehaya amet debdabe/   A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...
Yehaya amet debdabe/ A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...Ethio-Afric News en Views Media!!
 
Abiy ahmed vs hailemariam desalegn
Abiy ahmed vs hailemariam desalegnAbiy ahmed vs hailemariam desalegn
Abiy ahmed vs hailemariam desalegnberhanu taye
 
Root of Politics Gamblers !/ Yepoletikaw serr qumartegnoch///
 Root of  Politics Gamblers !/  Yepoletikaw serr qumartegnoch/// Root of  Politics Gamblers !/  Yepoletikaw serr qumartegnoch///
Root of Politics Gamblers !/ Yepoletikaw serr qumartegnoch///Ethio-Afric News en Views Media!!
 
Reporter issue-1631
Reporter issue-1631Reporter issue-1631
Reporter issue-1631AmanuelEndale
 
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...berhanu taye
 
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)VogelDenise
 

Similar to Zethiopia Newspaper Jan 2014 (15)

Ende hagher eninegagher/...let us discuss as a country
Ende hagher eninegagher/...let us discuss as a countryEnde hagher eninegagher/...let us discuss as a country
Ende hagher eninegagher/...let us discuss as a country
 
Weyane violates own_constitution
Weyane violates own_constitutionWeyane violates own_constitution
Weyane violates own_constitution
 
Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...
Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...
Timeline Political situation in Ethiopia Amharic language, it is mainly up ab...
 
Why does the Ethiopian government EPRDF shouts ? Ehadeg slemn ychohal
Why does the Ethiopian government EPRDF  shouts ?  Ehadeg slemn ychohalWhy does the Ethiopian government EPRDF  shouts ?  Ehadeg slemn ychohal
Why does the Ethiopian government EPRDF shouts ? Ehadeg slemn ychohal
 
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articles
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articlesኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articles
ኦሮሞ እና አማራ በኔ መጣጥፎች አይስማሙም - Oromo and Amhara disagree about my articles
 
Ethiopian hailoch ethio news
Ethiopian  hailoch ethio newsEthiopian  hailoch ethio news
Ethiopian hailoch ethio news
 
News eda-eritrea
News eda-eritreaNews eda-eritrea
News eda-eritrea
 
Coment on-ato-girma- seyfu speeches, on x eth pm meles
Coment on-ato-girma- seyfu  speeches, on  x eth pm  melesComent on-ato-girma- seyfu  speeches, on  x eth pm  meles
Coment on-ato-girma- seyfu speeches, on x eth pm meles
 
Yehaya amet debdabe/ A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...
Yehaya amet debdabe/   A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...Yehaya amet debdabe/   A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...
Yehaya amet debdabe/ A letter memories of twenty years ago, Former Ethiopia...
 
Abiy ahmed vs hailemariam desalegn
Abiy ahmed vs hailemariam desalegnAbiy ahmed vs hailemariam desalegn
Abiy ahmed vs hailemariam desalegn
 
Root of Politics Gamblers !/ Yepoletikaw serr qumartegnoch///
 Root of  Politics Gamblers !/  Yepoletikaw serr qumartegnoch/// Root of  Politics Gamblers !/  Yepoletikaw serr qumartegnoch///
Root of Politics Gamblers !/ Yepoletikaw serr qumartegnoch///
 
Reporter issue-1631
Reporter issue-1631Reporter issue-1631
Reporter issue-1631
 
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...
The debate over jonas and the debate over his acceptance of the article on hi...
 
Joint statement on_the_election
Joint statement on_the_electionJoint statement on_the_election
Joint statement on_the_election
 
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)
042117 - APPEAL TO INTERNATIONAL GOVERNMENTS (Amharic)
 

Zethiopia Newspaper Jan 2014

  • 1. ዘኢትዮጵያ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82. Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com DC Mayor: 30 percent of African populations are from Ethiopia Birtukan Mideksa Page 11 “Ethiopian represents the largest African population in the District of Colombia, 30 percent of the African population is from Ethiopia. I can tell you that 30 percent of population is vibrant, vital, active, and engaged, Page 8 business leaders, are very involved in basic fabrics of our city.” Mayor Vincent C. Gray noted during his opening remarks at DC Addis Sister City Agreement ceremony የቀድሞ የኢት ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ መጽሐፍ ወጣ "እኛና አብዮቱ የሚለውና" የደርግን አፈጣጠርና የዘመኑን ታሪክ በዝርዝር የሚያወሳው መጽሐፍ ትላንት ጀምሮ ገበያ ላይ መዋሉን አሳታሚው የፀሐይ አሳታሚና አከፋፋይ ድርጅት ሼል አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ወንድሙ ለዘኢትዮጵያ ገልጸዋል። 450 ገጾች ያሉትን የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስን መጽሐፍ ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ በመጠኑ ቃኝቶታል። “ደርግ ባከናወናቸው ተግባሮች ወይም ባሳለፋቸው ውሳኔዎች በብዙዎቹ ላይ ተሳታፊ ከመሆኔም ባሻገር በዋናነት አብዮቱን ከመሩት የደርግ አባላት ውስጥ አንዱ ስለነበርኩኝ የደርግን ታሪክ ለመጻፍ ስነሳ ራሴን እንደዋና ምንጭ አድርጌ ወሰድኩኝ።... ከእስር ቤት ባልደረቦቼ በጽሑፍና በቃል እየወሰድኩ እኔ ከማስታውሳቸውና ከማውቃቸው ጋር በማገናዘብ ይህንን መጽሐፍ ለማዘጋጀት በቃሁ።” ገጽ 5 Mrs. Obama challenged the students to emulate Menbere's story With its network of supporters worldwide, Amnesty’s potential to secure Eskinder’s freedom is significant,.. The support we get as political prisoners is indispensible.” 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com dereje@zethiopia.com ሰው ወደደም ጠላም ህወሓት መለሾ ከነበረበት የበለጠ ጠንካራ ሆን ይቀጥላል አቶ ስብሐት ነጋ ገጽ 2 በእዚህ በኩል First lady Michelle Obama, left, Bell Multicultural High School alumni , Ethiopian American Menbere, Assefa, center, and Education Secretary Arne Duncan look to an audience member asks a question at Bell Multicultural High School in Washington, Tuesday, Nov. 12, 2013. First lady Michelle Obama spoke to students about committing to education to create a better future for themselves and their country. (AP Page 11 Photo/Carolyn Kaster) ተመድ- የአዲስ አበባ ህዝብ ከ10 ዓመት በኋላ 12 ሚሊዮን ይገባል ገጽ 4 የዲሲ መንግሥት ባለታክሲዎችን እያማረረ ነው የሕብረተሰባችን ምሶሶ የሆኑትን በርካታ የታክሲ ባለቤቶችና አሸከርካሪዎችን እየተጫነ ያለው የዲሲ መንግሥት (ታክሲ ኮሚሽን) አዳዲስ ደንቦችና አሠራር አነጋጋሪ ከሆኑ ሰንብተዋል። ይህን አስመልከተው በግላቸው ጽሁፎችን በማቅረብ ሌሎችንም በማስተባበር በጉዳዩ ዙሪያ እየንተቀሳቀሱ የሚገኙትን አቶ ዓለሜ ታደሰን ዘኢትዮጵያ አነጋግሯል። አቶ ዓለሜ በNPR እና WTOP ሬዲዮ በመቅረብ በታክሲ ነጂዎች በኩል ያለውን ብሶት በማሰማት የድርሻቸውን ለማድረግ ሞክረዋል። የውል መፈረሚያው ቀን እንዲራዘም እስከ 500 ፊርማ አሰባስቦ በመጠየቅ ፣የታክሲ ካብ ኮሚሽኑ መረጃ አሰጣጡን በተሻለ መንገድ ለታክሲ ነጂዎች እንዲያቀርብ በማስገደድ፣ መረጃውንም በText message እና በ dctg.org (DC taxi group) ድረ ገጽ ሀሳብና መረጃ መለዋወጫ እንዲሆን ጥረት አድርገዋል። በአብዛኛው በሳቸው ከተነገረንና ከሌሎቹም ያጠናቀርነውን አስተያየት እነሆ አቅርበነዋል። ገጽ 4 ቴዎድሮስ ምትኩ አረፈ በሙዚቃ የተቀነባበሩ እውቅ ዜማዎችን ሲያስደምጥ የኖረው የሳክስፎን ተጫዋቹ ቴዎድሮስ ምትኩ ዲሴምበር 22 ህክምናውን ሲከታተልበት በነበረው በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። በግል እኔና አንቺ፣ አማሌሌ፣ እሹሩሩና የመሳሰሉትን ዜማዎች በአልቶ ሳክስ አሳምሮ የተጫወተው ቴዎድሮስ ምትኩ፣ ከ1960ዎቹ ጀምሮ በሙዚቃው ዓለም የኖረ ነው። ከእነ አለማየሁ እሸቴ ጋር በሶሌክስ ባንድ ኋላም ደመራ ባንድን የዶክተር አምሳሉ አክሊሉ ቀብር ተፈጸመ ጨምሮ ከተለያዩ የሙዚቃ ቡድኖች ጋር ተጫውቷል። ጥላሁን ገሠሠንና አስቴር አወቀ እንዲሁም ከወንድሙ ተሾመ ምትኩ ጋር ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ በትንፋሹ ሲያዜም ኖሯል። በተለይም በቨርጂኒያ ባቲ ሬስቶራንት የወንድሙ የተሾመ ምትኩን እነ ጋራ ሼር ነው ቤትሽ፣ ሞት አደላድሎ አፈር ሳይጫነኝ፣ የዘመዴ ባዳና ሰማይ ሲላወስ የመሳሰሉትን ዘመን ተሽጋሪ ጣፋጭ ዜማዎችን አስውቧል። በተለይ በ1987 አካባቢ ያወጣው በሙዚቃ መሳሪያና በሱ ትንፋሽ ብቻ የተቀነባበረውን አልበሙ የትም መቼም እሚደመጥ ሆኗል። ከአንጋፋው ጥላሁን ገሠሠ ጋር እህትማማቾን ያገቡ ወዳጆች ሲሆኑ ከባለቤቱ ወ/ሎ መዓዛ በዙ ጋር ከ20 ዓመታት በላይ በበትዳር አብረው ኖረዋል። ያልተወደደው ኑሮ ውድነት እኚህ ሰው ካሁን በኋላ የሚያስለቅሱት እንጂ የሚያለቅሱለት ሰው ላይኖር ይችላል። የዚህን እንባ ምንጭና ሚስጥር መመርመር ብቻውን አይበቃም። መኮንኑ አልቅሰው ቀና ሲሉ ስለመጪው ምን ሊያስቡ እንደሚችሉም መገመት ይገባል። ለዚያ ግምት የሚበቁ በቂ ምልክቶች አሉ። ምልክቶቹ ምንድናቸው? ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ = ወታደራዊ ሓርነት ትግራይ (ወሓት?) እየሆነ ይሆን? ድርጅቱ ህወሓት ቀድሞሞ "ህዝባዊ" አልነበረምና ለትግራይ ህዝብ አይቆምም። ከትግራይ ግን ለድርጅቱ የሚቆሙ ተጠቃሚ ዜጎችን አፍርቷል። እነዚያ ዜጎች ሲቪልም ይሁን ወታደር ካሁን በኋላ ለድርጅታቸው ዘብ ይቆማሉ። ወታደሮች ይሆናሉ። ይማራሉ፣ ይሰለጥናሉ፣ ይነግዳሉ፣ ይበለጽጋሉ በሁሉም ዘርፍ ብቃት ባለው መልክ ይደራጃሉ። በፍጹም ይሉኝታ አይኖራቸውም። የላቁት ወታደራዊ ማዕረጎች በሙሉ የእነሱ ይሆናሉ። ከወታደሩም ወደ ሲቪል መ/ቤቶች ተመድቦ መዛወር ይቻላል ተብሏል። ለዚህ ሲባል ቀጭን ትዕዛዝ ይወጣል። ህገመንግሥቱ ለነሱ ተብሎ ይለወጣል። አዋጆች ይወጣሉ። ልዩ በጀቶች ይፀድቃሉ። በዚያች አገር ያለነሱ ማንም እንደሌለ የአምሳና የመቶ ዓመት እቅድ ያወጣሉ። ይህን ኃላፊነት በበላይነት ለመምራት መለሾ ዜናዊ ለራሳቸው ሲሉ አደራጅተውት የሄዱት ሠራዊት እየተነቀሳቀሰ ነው። የመጀመሪያ ዓላማው ወታደራዊ መንግሥት መሆን ነው። እስካሁን ካልሆነ ማለት ነው። ሠራዊቱ የራሱ ምክር ቤት መሳይ፣ የራሱ ደህንነት፣ የራሱ ፖሊስ፣ ፣ የራሱ የቴሌኮሙኒኬሽንና የራሱ የቢዝነስ ተቋም እያቋቋመ ፣ የልማት መርሃ ግብሮችን እያወጣ ይመስላል። የፖለቲካ ድርጅቱ ሳስቶ እሱ እየፋፋ ነው። ገጽ 2 የኢትዮጵያውያን እንባ! በእንግሊዝኛ-አማርኛ መዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው የሚታወቁት ዶክተር አምሳሉ አክሊሉ የቀብር ሥነ ሥርዓት በየካ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ አማርኛ፣ ግእዝ፣ እንግሊዝኛ፣ አረብኛ፣ ጀርመንኛ፣ ጣሊያንኛና እብራይስጥ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው የሚናገሩት ዶክተር አምሳሉ፤ የእንግሊዝኛ-አማርኛ መዝገበ ቃላት፣ የጀርመንኛአማርኛ መዝገበ ቃላት፣ የአማርኛ ፈሊጦች፣ አጫጭር ልቦለዶች፣ “ጥሩ የአማርኛ ድርሰት እንዴት ያለነው?” የመሳሰሉት ለህትመት አብቅተዋል። ”የኢትዮጵያ ገጽ 9 ግ ፉ ገ ና ነው! “ኑሮ ተወዷል” ያልተባለበት ቀንና ዓመትን ለማስታወስ ከማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። ግን ሰው እየኖረ ነው! ምንድነው ተአምሩ? ሰው እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ለጊዜው ማወቁ ይቸግር ይሆናል። መንግሥት የሚያደርገውን ግን መመልከት ይቻላል። መንግሥት ምን እያደረገ ነው? የሚያደርገውንስ እስከመቼ ያደርገዋል? ህዝቡ ግን ኑሮውን እየገፋ ኑሮውም እሱን እየገፋው ነው። ገጽ 14 ገጽ 7
  • 2. ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com ግብፅን ወሓት? ያየ! ህወሓት ወደ (ወታደራዊ ሓርነት ትግራይ) 2 ጄነራሎቹ ሥልጣን ገንዘብ ጠመንጃ "መለሾ ድርጅቱን አልገደለውም በህይወቱ ነው ያለው ግን ይጠነክራል!" አቶ ስብሐት ነጋ የአቶ መለሾ ሞት በተሰማበት ምሽት አቶስብሐት ሥልጣን ላይ ከሌሉ ተራ አባል ከሆኑ በየትኛው ኃላፊነታቸው ነው ወደ ደህንነት ጽ/ቤት ሮጠው የሄዱት? ሼል አስፈጻሚው ስብሰባው ላይ የተገኙት? ወይ ያሉት ነገር ልክ አይደለም? ወይ እንዳሉት ተራ አባል አይደሉም። ከሁለት አንዱ ልክ አይመስልም። ወይም ሁለቱም ውሸት ሊሆን ይችላል። ወይስ እንደሚባለው ሌላ ስውር መዋቅር አለ ማለት ነው? 34 ጄኔራሎችን ሹሞያደረው ዓይነት መዋቅር? ከመለስ ሞት በኋላ ሥልጣን እየተቆለላቸው ከጠ/ሚኒስትሩም በላይ እየሆኑ ያሉት ጠ/ ኤታማዦር ሹሙ ጄ/ል ሳሞራ በቻይና የጠ/ሚኒስትሩን ዝቅ የጠ/ ኤታማዦር ሹም ሥልጣንና ተግባርን ደግሞ ከፍና ለየት ባደረገው የሰሞኑ አዲሱ አዋጅ አማካይነት እነዚህ ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል፦ ከጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ሥልጣናት 1. የመከላከያ አዛዦች ካውንስልን ይሰበስባል፣ ሥራዎቹን ያስተባብራል፣ የውሳኔዎቹን ተግባራዊነት ይቆጣጠራል 2. የጦር ኃይሎች ጠቅላይ መምርያን በበላይነት ይመራል፣ 3. የአገር መከላከያ ሠራዊትን ያደራጃል፣ ሠራዊቱን በማንኛውም ጊዜ ለውጊያ ብቁና ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ 4. የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ (ጠቅላይ ሚኒስትሩ) መመርያና ውሳኔን መሠረት በማድረግ ሠራዊቱን ያዛል፣ ያዋጋል፣ 5. ጠ/ ሚኒስትሩንና የመከላከያ ሚኒስትሩን በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ያማክራል፡፡ (4ኛውን ይህ ይቃረነዋል የታዛዥ አማካሪ?) 6. ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ድምፅ የመስጠት መብት የማይኖራቸው የሠራዊቱ ልዩ ልዩ አዛዦች በካውንስሉ ስብሰባ እንዲሳተፉ የማድረግ ሥልጣንን ይኖረዋል፡፡ (የካውንሱሉ አባላት በሠራዊቱ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ዕዞች ዋና አዛዦች፣ የአየር ኃይል ዋና አዛዥና የፕሪንሲፓል ስታፍ ዋና ኃላፊዎች፣ የአዛዦች ካውንስል አባላት ናቸው።) 7. የወታራዊ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት ለካውንሱሉ አቅርቦ ያስፀድቃል፡፡ “አብሬያቸው ጎልፍ ክለብ ስጫወት እውላለሁ” ስለሚሉት ሿሚና ተሿሚ ጀኔራሎች ሹመት አቶ ስብሐት አለማወቃቸው ያስገርማል። ተከትሎ የሚመጣባቸውን ጥያቄ ከመጋፈጥ ይህን አለማወቅ የሚያዋጣ ሆኖላቸዋል። መንግሥት ተጠሪነቱን ለመከላከያ ሚኒስቴር አድርጎ በአዋጅ ያቋቋመውን ወታደራዊ የቢዝነስ ኢምፓየር ስብሐት ወታደራዊ ሳይሆን ሲቪል መሆኑን ተናግረዋል። “እንዲህ ያለ ልዩነት ቢኖርማ ድርጅቱ ለምን እለቃለሁ ለማስተካከል ድርጅቱ ውስጥ እቆይ ነበር” ካሉ በኋላ ወረድ ብለው ደግሞ “እንዲህ ያለ ልዩነት ካለማ ለምን እቆያለሁ ድርጅቱን እለቅ ነበር አሁንም ከድርጅቱ አልወጣሁም... ያሉበትን የአቶ ስብሐት ነጋን የዘኢትዮጵያ ጋዜጣ ቃለ መጠይቅ በከፊል ከወራት በፊት በድህረ ገጾች አስደምጠነዋል። ጥያቄ አይፈሩም የሚባሉት ስብሐት ያመኑበትን መልሰው ካልመሰላቸውም ክደው ካልሆነላቸውም የጠያቂውን ሰዓት ቆርጠው መገላገል የሚችሉ ናቸው። ለተቃዋሚቻቸው ሲሆን ነገራቸው ፊት ለፊት ነው። ጥላቻቸውን አይደብቁም። ስለቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ያላቸውን ጥላቻ ቂም ባልረበደ ቁጣቸው ገልጸዋል። ሾለ አቶ መለስና ባለቤታቸው ወ/ሎ አዜብ ግን ቀለል ያለ የውስጥ ጠብ ነው ዓይነት አመላለስ ተጠቅመዋል። ሾለ ኢትዮጵያ ታሪክም አንጻር የሚያውቁትን ባይሆንም የሚያምኑበትን በመናገር ደፋር ናቸው። በቃለመጠይቁ ወቅት ለምሳሌ እንዲህ ብለዋል "ከታሪክ አንጻር ስናየው እንደገና ይታይና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያስተካክለው የታሪክ ቴስት ያለው (ከህወሓት ሌላ) ማነው? በኢትዮጵያ የነበረውን የታሪክ ተቃርኖ (ኮንትራዲሽን) ማን አወጣው? ለማመን የማይፈልግ ግን ይህን ለማየት የማይፈልግ ብቻ ሳይሆን ለማየት አይችልም። አሁን መስፍን ወልደማርያም ህወሓት ኢትዮጵያዊ ነው ሊል አይችልም። አቅም የለምው። ማንበብ አይችልም....ምክንያቱም ታሟል! አቶ ስብሐት የተዳከመውን ድርጅታቸውንና ፈርጥሞ የወጣውን ሠራዊታቸውን በማግባባትና በመሸምገል ሼል መጠመዳቸው ይነገራል። ከስብሐት ነጋ ቃለ መጠይቅ በከፊል ዘኢትዮጵያ - ወደ አሜሪካ ለምን መጡ ? አቶ ስብሐት- ወርልድ ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ ዓመታዊ በዓል አለ፡፡ ለዚያ ነው የመጣሁት። አቶ ስብሐት- ወረቀት ጽፌኮ ነው! ወረቀት ጽፌ የአሁን ማዕከላዊ ኮሚቴ ምርጫ እጩነት አልቀበልም። ተራ ሆኜ ለመታገል ነው የምፈለገው ብዬ በእጄ የጻፍኩት ነው። እና እኔ እዚያ ስለነበርኩ ማመልከቻ ጽፌ ለአለቃ ጸጋዬና ቴዎድሮስ ሓጎስ..እና ሶስት ጊዜ አመልክቼ ነበር ከዚያ በፊት አልተቀበሉትም። ሶስት ጊዜ ጽፌ ነው በአራተኛው ተቀበሉት። ዘኢትዮጵያ - መለሾ እያሉ ማለት ነው? ዘኢትዮጵያ - ማንን ወክለው ነው የመጡት ? አቶ ስብሐት- አዎ! አቶ ስብሐት- ውጋገን ባንክ የፕራይቬት ባንክ ነው። እሱን ወክዬ ነው። የቦርዱ ቼር ማን ነኝ። ዘኢትዮጵያ - ለምንድነው? ዘኢትዮጵያ - የኢህአዴግ አባል ነዎት አሁን? አቶ ስብሐት- የኢህአዴግ አባል የሚባል የለም የኢህአዴግ አባል ድርጅት ነው፡፡ የሕወሃት አባል ነኝ። ዘኢትዮጵያ - በድርጅቱ ተራ አባል ነዎት? የአባልነት ደረጃዎ ምንድነው? አቶ ስብሐት- ተራ አባል ነኝ። ዘኢትዮጵያ - እንግዲህ ድርጅቱን መሠረቱ ከሚባሉት ሰዎች ነዎት በአንድ ወቅትም ድርጅቱን በሊቀመንበርነት መርተዋል እየወረዱ መጥተው አሁን ተራ አባል ነው የሆኑት፣ አወራረድዎ እንዴት ነው? አቶ ስብሐት- ስለዚህ ከዚያ በፊት ያመለከትኳቸው በእድሜ ቢሆን ኖሮ ልወርድ እችል ነበር። ዘኢትዮጵያ - አዎ ግን መለሾ እያሉ ነው ከማዕከላዊ ኮሚቴ የወረዱት! አቶ ስብሐት- አዎ በማመልከቻ ነው አንድ ነው እነስዬ የወጡበትን? እነሱንም ጨምሮ? አቶ ስብሐት- አዎ የተባረሩ ናቸው። ዘኢትዮጵያ - እነስዬም....? አቶ ስብሐት- አዎ መካፈፋል አይደለም። እነሱኮ ተባረሩ! መባረር ነው። ሁል ጊዜ የሚባረር አለ ደረጃው የሚቀንስ አለ። ስለዚህ መከፋፈል የነበረው በ73 ዓመተ ምህርት በኛ በነግድይ ዘር ዐጽዮን በነበረበት ጊዜ። ዘ ኦንሊ ታይም ስለፕሮግራም ጥያቄ በህወሃት ጥያቄ የተነሳ ያኔ ብቻ ነው። እንጂ ህወሃት ከተፈጠረ ጀምሮ የፕሮግራም ጥያቄ አወዛጋቢ ሆኖ አያውቅም። የሚከፋፍል የፕሮግራም ጥያቄ ነው ወይም የአደረጃጀት ጥያቄ ነው። ተቋሙ ማለት ነው። እና በአሠራር ደረጃም በፕሮግራምም ብትል የሚከፋፍል ነገር የለም። የሚከፋፍል ፕሮግራም ነው ሌላ ነገር ሊመጣ አይችልም። እና ማንኛውም ሀሳብ ልዩነት ሲመጣ በተራዘመ ሂደት ውይይት "(TPLF) ህወሓት ሰው ወደደም አልወደደም መለሾ ከነበረበት በጣም የጠነከረ ድርጅት ይሆናል።" ስብሐት ነጋ አቶ ስብሐት- በምርጫዬ ነው። ከሊቀመንበርነት ጽፌ ማመልክቻ አቅርቤ ነው። ዘኢትዮጵያ - ወይስ መተካካት በሚለው ነው? 8. ከውትድርና መሰናበት በሚገባቸው ወይም በፍላጎት ስንብት በጠየቁ ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ጉዳይ በመወያየትና የግለሰቦቹን አስተያየት ወይም ቅሬታ በማዳመጥ፣ የውሳኔ ሐሳብ ለጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ለሆኑት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል፡፡ አቶ ስብሐት- መተካካት አለ መተካከት ቢኖርም የግድ ስትሪክት የሆነ በዚህ ዓመት ትወጣለህ የሚል የለም። እኔ ሶስት ጊዜ አመልክቼ በአራተኛው ላይ.... 9. (ከእንግዲህ የሠራዊቱ አባላትን ወደ ሲቪል የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ማዛወር ይቻላል።) ዝውውሩ በአባሉ ስምምነት ካልሆነም በግዳጅ (በኤታማዡር ሽሙ) ይፈጸማል። አቶ ስብሐት- አይደለም ሊቀመበር የነበርኩት ድሮ ነው። 10. ከዚህ ቀደም ያልነበሩ የወታደራዊ ዓቃቤ ሕግ፣ የወታደራዊ ተከላካይ ጠበቃና የወታደራዊ ፖሊስ አደረጃጀቶችን መፍጠር የሚያስችል አዳዲስ አንቀጾች ተካተዋል፡፡ የኤታማዦር ሹሙ ሥልጣን እዚህም ላይ ከፍተኛ እንደሆነ ይገመታል። ዘኢትዮጵያ - ሊቀመንበር በነበሩ ጊዜም ነው? ዘኢትዮጵያ - ገባኝ ያኔ በምርጫ ነው የወረዱት ከሊቀመንበርነቱ? አረፍተ ነገርናትኮ! አቶ ስብሐት- በድርጅቱ ባህል ወደ ሥልጣን የሚመጣው በምርጫ ነው። ከተመረጠ ይመረጣል ካልተመረጠ ደግሞ ይወድቃል ማለት ነው። እኔ ተመርጬ ነው። ስወርድ ደግሞ በራሴ ነው በቃ ብዬ ለምኜ ነው። ዘኢትዮጵያ - የጻፉት? ምን የምትል ናት አንድ አረፈተ ነገር ከሆነች በቃልዎ ያውቋታል! ዘኢትዮጵያ - ለምን መልቀቅ ፈለጉ? ዘኢትዮጵያ - ያንን ያደረጉት አለመስማማት ስላለ ከድርጅቱ ጋር አንዳንድ ግጭቶች ስለነበሩ ነው ወይስ ራስዎ የሰጡት ምክንያት ነው ትክክለኛው? አቶ ስብሐት- በቃ እየተኩ የመጡ ወጣቶች ከኔ ይበልጣሉ። ያኔ መለሾ ነበር መለሾ ይሻላል ብዬ ተራ የፖለት ቢሮ አባል ሆኜ ነው ለምኜ ነው በማመልቻ ጠይቄ። አሁንም እንዲሁ ለአራተኛ ጊዜ አመልክቼ ነው። ዘኢትዮጵያ - አሁን ሲሉ አሁን የመጨረሻውን 2010 ላይ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቱ የወጡትን ማለትዎ ነው? አቶ ስብሐት- አዎ! ዘኢትዮጵያ - ግን ይነገር የነበረው በመተካካቱ መሠረት ነው። እርስዎ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎቹም አንድ ስምንት የምትሆኑ ናችሁ ወጣችሁ የተባለው ያኔ። አቶ ስብሐት- አይዶንት ኖ! (አላውቅም) ዘኢትዮጵያ - እንደሱ ነው የተባለው። አቶ ስብሐት- አዎ ሌሎቹም ወጥተዋል። ዘኢትዮጵያ - ግን ለህዝቡ የተነገረው መተካካት የሚል ነው የርስዎንም ጨምሮ። ስለዚህ እሱ ኢንፎርሜሽን ልክ አልነበረም ማለት ነው? የእርስዎም በፈቃደኝነት መሆኑ አልተገለጸም። እርስዎ ብቻ ነዎት በፈቃደኝነት የወጡት ወይስ ሌሎቹም ናቸው? አቶ ስብሐት- ነርኩህኮ “እኔ በአሁኑ ጉባኤ የማዕከላዊ ኮሚቴ እጩነት አልካፈልም። ተራ ሆኜ ለመታገል እፈልጋለሁ።” አቶ ስብሐት- ያለመስማማትማ ቢኖር ኖሮኮ እቆያለሁ በድርጅቱ ለምን እወጣለሁ? ያለ መስማማት ሲኖር ያውም ትቆያለህ ስምምነት ልታመጣ ትቆያለህ። ያለመስማማት አልፏል። ከአንጃው ጋር የነበረ ማለት ነው። ስለዚህ ባለመስማማት አይደለም። ፈልጌ የወጣሁት ነው። ይሄኮ ሺ ጊዜ የተጻፈ ነው አዲስ ነገር አይደለም። ዘኢትዮጵያ - ስለዚህ አንዳንድ ጽሁፎች እንደዚህ ይወጡ ነበር። በተለይ ከወ/ሎ አዜብ ጋር በተያያዘ አለመስማማት ነበራቸው የሚል ነገር። ከወ/ሎ አዜብ ጋር የነበርዎት ግንኙነት ምን ይመስላል? ጤናማ ነው? አቶ ስብሐት- አሁን ምንድነው መሰለህ፣ አንድ ነገር ከመጀመሪያው ልንገርህ። በ TPLF (ህወሃት) መካፈፈል የሚባል ነገር አጋጥሞ አያውቅም። TPLF has never been divided! ዘኢትዮጵያ - የመጨረሻውንም ጨምሮ ማለት ይደረግበታል። ሶስት ዓመት ይፍጅ አራት ዓመት ይፍጅ ...ይሄ መደባዊ ጥያቄ የሀብታም ገበሬ የሚለው እሱም ግደይ ብቻውን ነው የወጣው አንጃ የነበረው የፕሮግራም አይደለም የሥልጣን ነው እሱም ተባረረ ዜር ፎር መለያየት መከፋፈል የሚባል ነገር አጋጥሞም አያውቅም። በ TPLF አይተን አናውቅም። ሌሎችም ቢሆኑ የኢህአዴግ ድርጅቶች መከፋፈል የሚባል ነገር አልነበረም። የሀሳብ ልዩነት ግን አሁንም አለ። ብዙ የሀሳብ ልዩነቶች ግጭቶች አሉ። ዘኢትዮጵያ - ምናልባት በሰዎች መካከል ያለውን ልዩነት ለማለት ነው። ሰዎች ተከፋፍለው በፕሮግራም ግን አንድ ሊሆኑ ይችላሉ። ፕሮግራሙ አንድ ሆኖ ሰዎች ግን ተለያይተዋል። አይተናል። የድርጅት አመራር የነበሩ ሰዎች.... አቶ ስብሐት- ይባረራሉ እና እኔ ልዩነት አለኝ ብዬ አልወጣሁም፣ ከድርጅቱ ድርጅቱ ውስጥኮ ነኝ ያለሁት። ልዩነት ቢኖርማ ስልጣን ላይ እቆያለሁ። እንዲፈታ በመፍታት ላይ ሚናዬን እንድጫወት። እኔ ድርጅቱን አምኜ ተራ ሆኜ ብታገል ይሻለኛል። ዘኢትዮጵያ - ስለዚህ ከወ/ሎ አዜብ ጋር ተብሎ የሚነገረው ነገር በተደጋጋሚ... አቶ ስብሐት- አልሰማሁም እንደሱ ሰምቼ አላውቅም። ዘኢትዮጵያ -ከወ/ሎ አዜብ ጋር ችግር አላቸው.... ወደ ገጽ 3
  • 3. ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com ከአፍሪካ በእንስሳት 1ኛ የሆነች አገር ቆዳ ከውጭ መግዛት ጀምራለች። 3 የአዲስ አበባ ሕዝብ ስንት ነው? ተመድ- ከአስር ዓመት በኋላ የከብትን አገር ቆዳ ቸገረው 12 ሚሊዮን ይገባል ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር፣ ትገዛለች፣ አሁን ደግሞ የከብት ቆዳም ልትገዛ ነው! ከአፍሪካ በእንስሳት ሀብት 1ኛ የሆነች አገር ቆዳ ከውጭ መግዛት ጀምራለች። የከብትን አገር ቆዳ ቸገረው እንደማለት ነው። ደግሞ ይህን የሚለው ልሹ መንግሥት ነው። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያሉት የቆዳ ፋብሪካዎች በዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የበግና ፍየል ሌጦና ከ2 ሚሊየን በላይ የበሬ ቆዳ ይፈልጋሉ። እየቀረበላቸው ያለው ግን ከግማሽ በታች 17 ሚሊየን ሌጦና ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በታች የሆነ ቆዳ ሆኗል። በጥሬ ቆዳ አቅርቦትና ፍላጎት መካከል የ20 ሚሊዮን ክፍተት አለ:: በዚህ የተነሳ የቆዳ ፋብሪካዎች ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው ነው። የቡና ዋጋን መውደቅ በአለበት ሁኔታ ኢትዮጵያ ተስፋ ያደረግችበት የቆዳና ሌጦ ኤክስፖርትም ችግር እየመጣበት ነው። በግና በሬ ሲወደዱ አራጅ ጠፋ ቆዳው ከየት ይምጣ? በዚህ የተነሳ ሃገሪቱ ከዘርፉ የምትጠብቀውን ገቢ ማሳካት አስቸጋሪ መሆኑን የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንዱ ለገሰ መግለጻቸውን የመንግሥት ሚዲያዎች ሰሞኑን ዘግበዋል። ዋና ዳይሬክተሩ እንደሚሉት ቆዳ ፋብሪካዎቹ የሚፈልጉትን የጥሬ ቆዳና ሌጦ አቅርቦት የሚያገኙት 20 በመቶውን ከቄራዎች የተቀረውን 80 በመቶ ደግሞ ከህብረተሰቡ ነው። ህብረተሰቡ ደግሞ አቅቶታል። ከብት የሚያርደው በአመዛኙ የበዓል ወቅቶችን እየጠበቀ በመሆኑ አብዛኛዎቹ የቆዳ ፋብሪካዎች አቅማቸውን ሙሉ ተጠቅመው መስራት እንዳይችሉ አድርጓል። በዚህም በእንስሳት ሃብቷ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነቸውን ሃገራችንን ተሻግረው ጥሬ ቆዳና ሌጦ ፍለጋ ወደ ውጭ ገበያ ማማተር ጀምረዋል ። መንግሥት ግን እንደ ኢንደስትሪ ሚኒስትር ደኤታው አቶ ታደሰ ኃይሌ በመሳሰሉት ከፍተኛ ባለሥልጣናቱ አማካይነት በሰጠው መግለጫ ማስተባበል የያዘ መስሏል። ይህ የሆነው በእንስሳቱ ላይ በሚደርሰው የጤና ችግር እንጂ በኑሮ ውድነቱ አለ መሆኑን እየገለጸ ነው። ለፋብሪካዎቹ ከሚቀርበው ቆዳ ውስጥ 65 በመቶው ጥራት የጎደለው በመሆኑ ይጣላል በሚል ጉዳዩን ከጥራትም ጋር አያይዞታል። በሃገሪቱ የተዘረጋው የግብይት ስርዓት ከቆዳና ሌጦ ባለቤቶች ፋብሪካዎች ጋር እስኪደርስ ድረስ ከአራት በላይ የገበያ ሰንሰለቶችን በማለፉ ቆዳውን ለብልሽት የሚዳርገው መሆኑንም የሚኒስትር ደኤታው መግለጫ አመልክቷል። ይህን ለመቅረፍ ሲባልም የንግድ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን «የጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይት አዋጅ» አዘጋጅቶ መጽደቁን እየተጠባበቀ መሆኑም ተገልጿል። ለዘመናት የኖረው የገበያ ሰንሰለት እንደምን ሆኖ ቆዳውን ለድንግተኛ ብልሽት ሊያጋልጠው እንደቻለ ግን የሚኒስትሩ መግለጫ አላብራራም። እንዲያውም በተቀራኒው መንግሥት ከፍተኛ ጥራት እንዳለው ከሚነገረው ከኢትዮጵያ ቆዳና ሌጦ ላለፉት ዓመታት በዓመት 123 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ እያስገኘ መምጣቱን በመግለጽ፣ በ2007 ዓመት መጨረሻ በዓመት 500 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢን ለማግኘት እቅድ መያዙን ሲገልጽ መቆየቱ ይታወቃል። ይልቁንም ችግሩ የቆዳ ጥራት ሳይሆን እንደተባለው ህዝቡ በኑሮ ውድነት የተነሳ ከብት ማረዱን እየቀነሰ በመጣቱ የመሆኑን ግምት ያጎላዋል። የሆኖ ሆኖ ኢትዮጵያው ወደ 30 ለሚደርሱ የቆዳና ተያያዥ ፋብሪካዎቿ ቆዳንና ሌጦን ከውጭ ገዝታ ማስገባት ግዴታዋ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ጀምራለች። በዚህ የተቆጩትን የሞጆ ቆዳ ፋብሪካ ሾል አስኪያጅ አቶ ሬድዋን በዳዳ ለዘመን እንደገለጹት “በግ የሌላት ሶማሊያ እንኳን የበግ ሌጦ ወደ ውጭ ትልካለች።” ብለዋል። አገር ውስጥ ገዢ ያጡ ነጋዴዎችም ከወትሮው በላቀ ሁኔታ በግና ፍየሎችን በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ መንዳት መጀመራቸው ተሰምቷል። ጤፍ ኤክስፖርት አድርጎ እንጀራን እንደማስመጣት መስሏል። “The population of the capital Addis Ababa has doubled every decade since 1984 and UN-Habitat has predicted that the population will reach 12 million in 2024. ... “ ይላል አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል። ( የ The United Nations Human Settlements Programme (UN–Habitat)። 2014 ማለት የዛሬ 10 ዓመት ማለት ነው። በመሆኑም ይህን አሳሳቢ ችግር በጽኑ ልታስብበት እንደሚገባት የሚመክሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እየተሰሙ ነው። የኢትዮጵያ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣንም 5 ሚሊዮን አልፏል የሚባለውን የአዲስ አበባ ህዝብ ቁጥር በድፍረት ባይቀበልም ሲፈራ ሲቸርም ቢሆን ሾለ አጨማመሩ ማሳሰቡ አልቀረም። ዙሪያ ጥምዙን ሄዶ “የከተማ ህዝብ ቁጥር ዕድገት ወደፊትም እስካሁን ከታየው ባላነሰ ፍጥነት የሚቀጥል መሆኑን ለመገመት የሚያስችሉ መሰረታዊ መነሻዎች አሉ” ካለ በኋላ “ እ.ኤ.አ. በ2020 ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል 30% የሚሆነው በከተማ እንደሚኖር ይገመታል” ብሏል። ከተማ ማለት ምንድነው? አንድን ከተማ ከተማ የሚያስብለው ከህዝብ ብዛት አንጻር ስንት ሰው ሲኖርበት ነው የሚለውን መመለሾ አስፈላጊ ነው። ቤትና ሰው የሚቆጥረው ኤጀንሲው ግን አሁንም እሱን በቀጥታ ከመመለስ ኢትዮጵያ ውስጥ “2ሺ እና ከዚያ በላይ የህዝብ ብዛት ያላቸው ከተሞች 924 ናቸው” ይላል። ቀበሌውን ሁሉ ከተማ እያልን እንዳንቸገር ቢያንስ ከ100ሺ በላይ ነዋሪዎች ያሉባቸውን ከተሞች እንዲነግረን ብንጠይቅ ከኤጄንሲው የምናገኘው 13 ከተሞች ብቻ መሆናቸውን ነው። እንደ ኤጄኒስው ገለጻ ከአዲስ አበባ ቀጥላ በርካታ ነዋሪዎች ያሏት ሁለተኛ ከተማ ድሬዳዋ ናት። በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ከተማ መካከል ያለውን ልዩነት በ12 እጅ የሚበልጥ በመሆኑ በኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ያለው ልዩነት እጅግ የጎላ መሆኑን መረዳት እንችላለን ይላል መግለጫው። ዞሮ ዞሮ ኢትዮጵያ ያላት ከተማ አንድ እሱም ቢሆን አዲስ አበባ ብቻ ነው የሚሉ አሉ። እሷም ብትሆን በቂ መብራትና ውሃ ገና አላገኘችም። የአዲስ አበባ ቁጥር ግን ካለበት ሳይነቃነቅ 3ሚሊዮን እንደተባለ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው? በዚህ ስሌትስ እንዴት አድርጎ ነው የዛሬ አስር ዓመት 12 396 ከመቶ ? መንግሥት ለልሹ አጨበጨበ 198 ሺ 667 ዜጎቹን ኤክስፖርት አድርጓል! ባለፈው ዓመት፣ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2005 የበጀት ዓመት፣ “40,000 ዜጎችን በውጭ አገር ሼል ለማሠማራት አቅዶ ለ198 ሺ 667 (10 ሺ736 ወንዶች እና 187ሺ 931 ሴቶች) አገልግሎት በመስጠት ከእቅድ በላይ 396 በመቶ አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡” ሲል የመንግሥት የአምስት ዓመት የእቅድና ትራንስፎሜሽን አፈጻጸም ሪፖርት አመልክቷል። “አፈጻጸሙ ከባለፈውም ዓመት ጋር ሲነጻጸር እጅግ በጣም ከፍ ያለ” መሆኑን ገልጾ “በ2007 በ2013/14 የበጀት ዓመት እንደሚደረስበት የተጣለው ግብ ሙሉ በሙሉ ተደርሶበታል፡፡” ብሏል። መንግሥት ይህን ይበል እንጂ ሰሞኑን ከሳዑዲ አረቢያ ብቻ ከ100ሺ በላይ የሚሆኑ ተመላሽ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ማጓጓዙን እየገለጸ ነው። እንኳንስ የዜጎቹ መብትና ደህንነት ሊከበር በተቃራኒው ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰውና አሳዛኝ ግፍ የተፈጸመባቸው ዜጎችን ሲያጓጉዝ ተገኝቷል። የስደት ተመላሾቹንም መልሶ በማጓጓዙ ከፍተኛ አድናቆት እንዲሰጠው የሚጠባበቀው መንግሥት ይህንንም ከእቅድ በላይ ማከናወኑን ገልጿል። 10ሺ ሰዎችን ለመመለሾ አቅዶ 10 እጥፍ የሚደርሱትን ከ100ሺ በላይ ኢትዮጵያውያንን መልሶ ለማጓጓዝ በመቻሉ ተኩራርቷል። በውጭ ሃገር ለሼል የሚሠማሩ ዜጎች፣ መብትና ደህንነትን ለማስጠበቅ፣ እንዲሁም ህገ ወጥ የሠዎች ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል፣ አንድ ብሄራዊ ኮሚቴ መቋቁሙን ሪፖርቱ አስታውሷል። በተለይ የሰዎች ህገ ወጥ ዝውውርን በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንዲቻል በውጭ አገር ለሼል የሚሠማሩ ኢትዮጵያውያንን መብት ደህንነትና ክብር ለማስጠበቅ ከፌዴራል በተጨማሪ በየክልሉ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ ማድረግ ናቸው፡፡ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀን ወደ 800 የሚደርሱ ወደ አረብ አገራት ተጓዥ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ፈቃድ በመስጠት ያስተናግድ እንደነበረ መግለጹ ይታወሳል። የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሸለመ “ሠራተኞችን ወደ ውጭ በሕጋዊ መንገድ ከሚልኩ 178 ያህል ኤጀንሲዎች ጋር በጋራ እንደሚሠሩና ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኩዌትና ዱባይ ከገጽ 2 ስብሐት አቶ ስብሐት- እኔ ችግር ካለኝ ከሷ ጋር ነው የምነጋገረው እንጂ... ዘኢትዮጵያ -ግንኙነትዎ ጤናማ ነው? አቶ ስብሐት- ኸ? ዘኢትዮጵያ ግንኙነትዎ! -ጤናማ ነው አቶ ስብሐት- እንዴ አንድ ድርጅት ውስጥ ነውኮ ያለነው። ይሄ የሥራቤት ድርጅትኮ አይደለም። አንድ ጊዜ ተጣልተህ በሀሳብ ከተለያየህ ትወያይበታለህ። የሀሳብ ልዩነት ብዙ ሰዎች አለን። እነሱም ከኔጋር አለ..ስለዚህ ይሄ ፀጋችን ነው። ንቁ ኃይላችን እሱ ነው። ይሄ ባይኖር ነው ይሄ ስላለ ያለሞከራረፍ ውይይት ስለሚደረግ ነው TPLF ሁለትም ሶስትም ሆኖ የማያውቀው። በዚህ በሀሳብ ልዩነት መወያየት የተቸገረ ይባረራል። በአንጃ ጊዜም ያየነው እሱ ነው። ረገጡ! ትልቁ ሪሜርሾ ትልቁ ሀብት የተለያዩ ሀሳቦችን ማስተካከል ይሄ ነው አቅማችን። ከመጀመሪያው ብረት አልነበረም። ስለዚህ ይሄ የድርጅት አሠራርና ከህዝብ ጋር ያለን ግንኙነት። That was the መድረክ that was the ጥይት በውስጣችን የነበረው ዴምክራቲክ ሕይወት ነው ይሄ የሚያደናቅፍ ይባረራል። እና እኔ አሁን የጠየቅከው የሀሳብ ልዩነት ይኖራል። ኤፈርት እንደዚህ ይሁን ይሄ እንደዚህ ይሁን ያ ሀብታችን በረዶ የገባበት አይደለም። ትኩስ ነው። ሕይወት አለው። ፖለቲካዊ ህይወት ሁልጊዜ ትኩስ መሆን አለበት። ትኩስ ካልሆነ ትበላሻለህ። ከውስጥም ከውጭም ኮሚኒኬሽን መኖር አለበት ንፋስ። እኔ አሁን ያልከው ያነሳኸው አንተ..... ዘኢትዮጵያ - አለመስማትዎ ግን ይገርማል ምክንያቱም የእርስዎና የወ/ሎ አዜብ የሚባለው ነገር ደጋፊዎችም ሳይቀሩ ቀላል ነገር አይመስለኝም። ምክንያቱም ለረጅም ጊዜ የነበረ ነገር ነው። እንዲያውም ወደ ቡድናዊ ደረጃ የአዜብ ቡድን የአቶ ስብሐት ቡድን እየተባለ የሚጻፍ የሚነገር በደጋፊው በተቃዋሚው ውስጥ የሚሰማ ነገር ነው። አቶ ስብሐት- ሊኖር ይችላል! ዘኢትዮጵያ - እና አለመስማትዎ ገርሞኝ ነው! አቶ ስብሐት- የሚሰማው ነው እንትኑ። ይሄ የሚሰማ ጅል መሆን አለበት። የሀሳብ ልዩነት ይነሳል ወይ አይነሳም ይነሳል? እሱ ነው ህይወታችን ይነሳል። ሺ ጊዜ ተገልጿል። የውስጥ ፖለቲካዊ ሕይወት መኖር አለበት! ዘኢትዮጵያ -የሀሳብ ልዩነት ሲነሳ ያፋጫል ብዙ ጊዜ፣ አንዳንዴ ከድርጅትዎ እስኪባረሩም ድረስ ያስኬዳል፤ እስከምንድረስ ነው የሄደው የርስዎ የሀሳብ ልዩነት? አቶ ስብሐት- እስከ ተፋጭቶ እስኪታረቅ ድረስ። እሱኮነው መጨረሻው ተፋጭቶ አልተለያየንም። ተፋጭቶን እስኪያቀራርበን ሄደ። ዘኢትዮጵያ - ይሄ ስጋት ነበረ? እርስዎ የሰጉበት ጊዜ ነበረ በድርጅቱ አካሄድ ላይ ድርጅቱ ሳስቷል ድርጅቱ አደጋ ላይ ወድቋል ያሉበት ጊዜ ነበር? አቶ ስብሐት- ስላልወደቀ ብዬ አላውቅም። ዘኢትዮጵያ - ምልክቱንም አላዩትም?! ችግር የደረሰበትን ጊዜ? (አቶ ስብሐት ድርጅቱ አደጋ ላይ ወድቋል እያሉ ከድርጅቱ የተሰናበቱ ሰዎችን ሳይቀር እየዞሩ ያነጋግሩ ለማግባባት ይጥሩ እንደነበር ሲነገር የኖረ ነው።) አቶ ስብሐት- አንዳንድ ድክመቶች ነበሩ። እሱ አሁን ወደ ገጽ 4 ሚሊዮን የሚደርሰው? ቁጥር ትክክል ካልሆነስ የአዲስ አበባ ቁጥር ሁልጊዜ አንሶ እንዲነገር የሚፈለገው ለምንድነው? እነዚህ ጥያቄዎች ጉዳዬ የተባሉ አይመስልም። አሁንም ከሱ ከቁጥሩ ይልቅ ስለችግሩና አደጋው ማውራቱ የቀለለ መስሏል። ብዛቱ አስከትሏል የተባለው ችግር እየተወራ የብዛቱ መጠን የሚደበቀው ለምንድነው? የማ ዕከላዊ ስታትስቲክስ ስለችግሩ ሲወራ የሚከተለውን ብሏል፦ “ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየውና ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ከፍተኛ የህዝብ ፍልሰት የከተማው ኢኮኖሚ ያለውን ነዋሪ መሸከም በማይችልበት ሁኔታ ላይ እያለ የተከሰተ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ባለው ውስን ቁሳዊና ተቋማዊ አቅም ዘላቂ ልማት ለማምጣት ተቸግሯል፡፡ በመሆኑም በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የከተማ ህዝብ ዕለታዊ ፍላጎት ለማሟላት አዳጋች ሆኗል፡፡ ከዚህም የተነሳ የአዲስ አበባ ከተማ፣ ድህነትና ሾል አጥነት የተንሰራፋባት፣ የተዳከመ የመሰረተ ልማት አውታር የሚገኝባት፣ የተጨናነቀ የመኖሪያ አካባቢና ከደረጃ በታች የሆኑ ግንባታዎች የተሞላች፣ ቀላል የማይባል ቁጥር የያዘ ነዋሪ መደበኛ ባልሆነ የስራ መስክ ተሰማርቶ የሚገኝባት፣ የጎዳና ተዳዳሪነት፣ ዝሙት አዳሪነት፣ ልመናና ወንጀለኛነት፣ የትራፊክ አደጋ፣ የንብረት ቃጠሎና ውድመት፣ ሕገወጥ ግንባታ ወዘተ የተንሰራፋባት መሆኗ ተጠቃሽ ነው፡፡” በአንድ በኩል ሾለ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እየተወራ በሌላ በኩል በአሃዝ ሳይሆን በአይነት ስለሚገለጽ እንደዚህ ያለ ችግር የማውራት ፖለቲካ ግልጽ አይደለም። የኢኮኖሚ እድገት ሲወራ ለእድገቱ አስተዋጽኦ ያለውን የአምራች ህዝብ ቁጥር መጨመር ለመሸሸግ ተፈልጎ ከሆነ ኢኮኖሚስቶች እዚህ ላይ ቢያጫውቱን ከተሳካላቸውም ቢያስጠነቅቁን ጥሩ ነው። 10 ዓመት ቅርብ ሲሆን የተባለው 12 ሚሊዮን ደግሞ ብዙ ነው። ከአዲስ አበባ ህዝብ መውለድ በሚችል የዕድሜ ክልል የሚገኘው 64 ከመቶ በላይ ነው መባሉ ከግምት ሊገባ የሚገባው ነው። የወንድና የሴቱም ቁጥር የሚለያይ ሲሆን የሴቶች ቁጥር ከወንዶች ቁጥር ጋር ሲወዳደር በ16 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ 84 ወንዶች ለ100 ሴቶች ይደርሳሉ ማለት ነው። ብዙ ወላድ አለ! በሕጋዊ መንገድ ሠራተኞችን እንደሚልኩ” መናገራቸው በወቅቱ ተዘግቧል፡ ፡ እንዲያውም የተጓዡ መጠን እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ መንግሥት ቶሎ ቶሎ መላክ እንዲችል፣ “ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ለችግሩ መፍትሔ ለማግኘት ቀደም ሲል ወደ ሌላ ቦታ ተዘዋውረው የነበሩ ሠራተኞቹን ሳይቀር በመመለስ ላይ ይገኛል፡፡ በምሳ ሰዓት፣ ቅዳሜና እሑድ ሳይቀር ሠራተኞች በእረፍት ቀናቸው እንዲገቡ እያደረጉ መሆናቸውን” ባለሥልጣኑ አስረድተዋል። ስለዚህ መንግሥት ከኤጄንሲዎች (ደላሎች) ጋር ተባብሮ ለሼል ወደ አረብ አገራት የሚልካቸውን ዜጎቹን ሲልክም ሆነ ሲመልስ በኩራትና በትጋት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል። ባለፈው ዓመት ብቻ 30ሺ 269 የውጭ ዜጎች ኢትዮጵያ ገብተው እየሠሩ ነው በተያያዘ ዘገባ በ2012/2013 በጀት ዓመት መንግሥት ለ23,000 የውጭ አገር ዜጎች የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት አቅዶ በድምሩ ለ30,269 የውጭ አገር ዜጎች የሥራ ፈቃድ የመስጠት አገልግሎት ማከናወኑን ገልጿል፡፡ አፈጻጸሙ ከዕቅዱ በላይ ሊሆን የቻለው በአገሪቱ በተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ እና እያደገ በመጣው የመሠረተ ልማት ግንባታ ምክንያት ለሼል ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የውጭ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ነው ብሏል። የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ! የሠራዊቱን ጡንቻ የሚያፈረጥሙ ሕጎች እየወጡ ልዩ ልዩ ሹመቶች እየተሰጡ ነው። በዚህ መሠረት የጄኔራል መኮንኖች ሹመትና በመከላከያ ሠራዊቱ አመራሮች ላይ የኃላፊነት ሽግሽግ ተካሄዷል፡፡ የሰሜን ዕዝ ዋና አዛዥ የነበሩት ሌተና ጄኔራል ሰአረ መኮንን በተሻለ ኃላፊነት ወደ ማዕከል እንዲመለሱ መደረጉ ታውቋል፡፡ በምትካቸው ሜጀር ጄኔራል ዮሐንስ ወልደ ጊዮርጊስ ተሹመዋል፡፡ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ በነበሩት ሜጀር ጄኔራል ሞላ ኃይለ ማርያም ምትክ ሜጀር ጄኔራል አደም መሐመድ መተካታቸው ተገልጸዋል፡፡ ከአየር ኃይል አዛዥነታቸው የተነሱት ሜጀር ጄኔራል ሞላ እንደ ሌተና ጄኔራል ሰአረ ወደ ማዕከል ለከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት መሾማቸው ተዘግቧል፡ ፡ ሹመቱን ተክትሎ የአገር መከላከያ ሠራዊት የሚተዳደርባቸውን የተለያዩ አዋጆች በአንድ ያጠቃለለና የተለያዩ ማሻሻያዎችን ያካተተ አዋጅ መዘጋጀቱም ተገልጿል። ( ለአብነት ያህል ጠ/ሚኒስትሩን በማስፈቀድ ከሚል ለበጣ ጋር የሚከተሉት መብቶች ለመከላከያ ተሰጥተዋል) • ከፌዴራል መንግሥት በየዓመቱ ከሚያገኘው በጀት በተጨማሪ፣ ከሌሎች የገቢ ምንጮች እንዲጠቀም በሕግ ተፈቅዶለታል። • በተቆጣጣሪ ባለሥልጣንነት የሚመራቸው የልማት ድርጅቶች በየዓመቱ ከሚያገኙት ትርፍ ላይ ድርሻ እንዲኖረው፣ ሕጋዊ ፈቃድ አግኝቷል፡ • በተለያዩ አገሮች የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ሠራዊቱን በማሰማራት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚያገኘውን ክፍያ (በውጭ ምንዛሪ) መጠቀም ይችላል። መከላከያ ሚኒስቴር ካሉት አትራፊ የልማት ድርጅቶች መካከል • የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን • ግዙፉ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ • የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝና • የመከላከያ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ኢንተርፕራይዝ ይኙበታል። ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ከሁለት ዓመት በፊት በአሥር ቢሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ግዙፉ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በተቋቋመ በሦስተኛ ዓመቱ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ እያንቀሳቀሰ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዓመታዊ ትርፍም እያገኘ ነው፡፡ መንግሥት በአጠቃላይ ለመከላከያ የሚፈቅድለት በጀት (ለምሳሌ በዚህ ዓመት) 7.5 ቢሊዮን ብር ቢሆንም ከበርቴው መከላከያ ግን ካሉት ድርጅቶች መካከል በአንዷ ብቻ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ ያንቀሳቀሳል።
  • 4. ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ Zethiopia Ethiopian American Community News NO.82 Jan 2014 202 518 0245 P.o.box 2049, Fairfax, VA 22031 www.zethiopia com ፍሬነገር “አለ”-የኢትዮጵያ ዎልማርት! ሁሉንም ነገር እንሸጣለን ሁሉንም ነገር እንገዛለን መንግሥት ሌላ አዲስ የንግድ ድርጅት አቋቋመ የኑሮ ውድነቱ እንዴት ተቻለ? መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ!? “ኑሮ ተወዷል” ያልተባለበትን ቀን ለማስታወስ ከማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። ሰው ግን እየኖረ ነው! ምንድነው ተአምሩ? ሰው እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ማወቁ ይቸግር ይሆናል። መንግሥት የሚያደርገውን ግን መመልከት ይቻላል። ለሠራተኞች ደመወዝ ጨምሯል፣ በሸቀጦች ላይ ጊዜያዊ ተመን አውጥቷል። ሕገ - ወጥ ነጋዴዎች ያላቸውን የመቅጣት እርምጃ ወስዷል። ያለቅጥ የሚሰጠውን የባንክ ብድር በመግታት ግሽበቱን ለመቆጣጠር ሞክሯል። ምንዛሪ በመሸጥ ከፍተኛ የሆነ የዶላር ክምችት ፈጥሯል፡ ፡ ከእነዚህ ሁሉ የላቀው ግን የኑሮ ዋልታ የሆነውን የእህል አስቤዛ ገዝቶ መደጎም ነው። መንግሥት ተጠሪነቱ ለንግድ ሚኒስቴር የሆነ የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት የሚባል ተቋም አለው። ሥራው ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ እህል እየሸመተ በርካሽ ዋጋ ለገበያ ማቅረብ ነው። እንደ መንግሥት እምነት ይህ ድርጅቱ እስካለ እህል እጥረት አይኖርም ፤ ዋጋም ርቆ አይሄድም። ለምሳሌ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኩንታል እስከ 800 ብር ደርሶ የነበረውን የስንዴ ዋጋ ወደ 580 ብር ጎትቶ ጥሎታል። ለእንዲህ ያለው ጨዋታ እስካሁን ከ18 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ስንዴ ከውጭ ገዝቶ አስገብቷል። ለምሳሌ አምና በ2005 ዓመተ ምህረት ብቻ 5.6 ቢሊዮን ብር ወጪ አድርጎ ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እሕል በመግዛት ገበያውን ዝም አሰኝቶታል። ለዳቦ ጋጋሪዎች የሚሆን ዱቄት ለሚያመርቱ ፋብሪካዎች 6 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ገዝቶ አድሏል። ከገበሬዎች ላይ ከ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል ገዝቷል። ድርጅቱ ዘንድሮ ከሀገር ውስጥና ከውጭ እህሉን ለመግዛት 4 ቢሊዮን ብር መድቦ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት በመላ አገሪቱ 10 ቅርንጫፎች እና ከ70 የማያንሱ የግዥ እና ሽያጭ ጣቢያዎች አሉት። እህል ገዝቶ (ወይም ከጎተራው አውጥቶ) ገበያው ላይ ለመርጨት አስቧል። ይህ መንግሥት በገበያው ላይ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት ያሳያል ብለው የሚተቹት አሉ። ከዚያም አልፈው እንዲያውም ለዋጋ ውድነቱ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ተጠያቂ ነው ብለው የሚከሱትም አሉ። ምክንያቱም መንግሥት ለበላተኞችም፣ ለአከፋፋዮችም፣ ለእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ሳይቀር እህል እየገዛ ስለሚሸጥ ብዙ እህል ያስፈልገዋል። ኪሳራም ስለማይኖርበት ከገበሬው በተጠየቀው ዋጋ ተሻምቶ ይገዛል። ከዚያ የሚያገኘውን ዶላር መልሶ እህል ይገዛበታል፣ በገዛውም እህል ገበያውን ያረጋገበታል። “ኢትዮጵያ በምግብ እህል ራሷን ትችላለች” ሲባል አምርታ ሳይሆን ገዝታ በመመገብ ነው መባሉም ለዚህ ነው። ገበያው ሰማይ ቢደርስ ግሽበቱ (ኢንፍሌሽኑ) ቢፈላ፣ መንግሥት የተወደደውን እያስረከሰ፣ የረከሰውን እያስወደደ ሚዛኑን እያጫወተ ይጠብቃል። ከውጭም ሆነ ከውስጥ፣ ጨው፣ ስንዴ፣ ዘይትና ቅመማቅመሙን ሲገዛ በአንድ ስሙ ወጥ ሠርቶ ማቅረብ ቀርቶታል። በዚህ ዓመት ካለው እቅዱ መካከልም 100ሺ ኩንታል ጤፍ፣ 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የስንዴና የቦቆሎ ምርት የመሳሰሉትን 7 ሚሊዮን ኩንታል ከገበሬው በመግዛት ገበያውን ለማጥለቅለቅ እቅድ ይዟል። ችግር ሲፈጠር ቶሎ ከኢትዮጵያ ትልቁን የእርሻ መሬት የገዙት ህንዶች ናቸው። ገዝታ የምታስመጣው ለመድረስ በሚል በአሁኑ ኢትዮጵያ ደግሞ እህል/ስንዴ ወቅት 8 ሚሊዮን ኩንታል ከህንድ ነው። በዚህ አመት መስከረም ወር ብቻ ከገዛችው 4 እሕል የማከማቸት አቅም ፈጥሯል፡፡ 40 ሚሊዮን ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታሉ ህዝብ ቢራብ ለ6ወር የተገዛው ከህንድ ነው። መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ! መቀለብ እችላለሁ ባይ ሆኗል። ለዚህም አሁን በመጠባበቂያ ክምችት ያለውን እንዲህም ሆኖ ኑሮ ውድነቱ በጅምላም ቸርቻሪም አስመጪም የ465 ሺሕ ሜትሪክ ቶን የእህል ቀጥሏል። እስከመቼ? ላኪም ስለሆነ በብዛት የተሳተፈበት ክምችት፣ ወደ ሦስት ሚሊዮን አይታወቅም። ቢሆንም ቢሆንም ንግድ ሀብታም አድርጎታል። ከአገር ሜትሪክ ቶን በማሳደግ፣ 40 ዛሬ...ሰው በልቶ ያድራል! ገዝቶም ውስጥ አልፎ ኤክስፖርት ለማድረግ ሚሊዮን ሕዝብ ለስድስት ወር ሆነ ተገዝቶ ወይም ፖለቲካው ቡናና የቅባት እህሎችንም መሸጥ መመገብ የሚያስችሉ የእህል ሌላው ነገር ሆኖ ማለት ነው! መጀመሩም ለዚህ ነው። ቡና እየላከ ማከማቻ ጎተራዎችን እየገነባሁ ነው በነገራችን ላይ ከኢትዮጵያ ትልቁን ስንዴ ለማስመጣት ተነስቷል። ብሏል። በቂ መብራት ሳይኖረው የእርሻ መሬት የገዙት ህንዶች ለጎረቤት አገሮች ኤሌክትሪክ መንግሥት በእህል ንግድ ድርጅት ናቸው። ኢትዮጵያ ደግሞ እህል/ ኃይል እሸጣለሁ እንደሚለው አማካይነት፣ እንኳን አገር ውስጥ ስንዴ ገዝታ የምታስመጣው ከህንድ እህልም ኤክስፖርት አደርጋለሁ ያለውን ፍጆታ ኢትዮጵያ ነው። በዚህ አመት መስከረም ወር ብሎ ተነስቷል። በነዚህ ምክንያቶች ወደ ውጭ በምትልካቸው ብቻ ከገዛችው 4 ሚሊየን ኩንታል መንግሥት ወደ ገበያ መርጨት የኤክስፖርት ምርቶች ላይ ሳይቀር ስንዴ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሳይሆን ከገበያም ይሰበስባል እጁን አስገብቷል። በዚህ ዓመት ኩንታሉ የተገዛው ከህንድ ነው። ማለት ነው። ገበያው ላይ እጥረት 56 ሺ ኩንታል የቡና ምርት መሬት ከኢትዮጵያ ስንዴ ከህንድ! መፈጠሩም ለዚህ ይመስላል። ልሹ ከገበሬው በመግዛት ወደ ውጭ ያቆሰለውን ገበያ ልሹ ያክመዋል። አገር ልኳል። 195ሺ ኩንታል የጥራጥሬና የቅባት እሕል በዚህ ዓመት 6.5 ሚሊዮን ኩንታል ምርቶችን ኤክስፖርት አድርጓል። የዲሲ መንግሥት ባለታክሲዎችን እያማረረ ነው የታክሲ ሼል እንዴት ነው? ታክሲ ጥሩ ሼል ነው። ገቢውም የተረጋጋ ኑሮ ለመኖር ያስችላል። በብዙ አንጻር ሕብረተሰባችንን የሚደግፉት ባለታክሲዎች ናቸው። ታክሲ ሼል ጊዜ እንደ አግባቡ ለመጠቀም ያስችላል። ልጅ ማሳደጊያ ጊዜ ይሰጣል። የታክሲ ባለቤትነት ማለት የንብረት ባለቤትነት ማለት አይደለም የገዛ ሕይወት ባለቤትነት ማለት ነው። በህይወት ውስጥ ትልቁ ሀብት ጊዜ ነው። በራስ ጊዜ መወሰንን የመሰለ ባለቤትነት የለም። አሁን ግን ያንን ባለቤትነቱን እያሳጡት ነው። “በተዘዋዋሪ ቅጥረኛ የሚያደርገውን ሕጎች አመጡ። ማሽኑ ታክሲው ላይ ይገጠማል። ያ ማሽን በምን ሰዓት የት እንደነበርክ ምን ያህል እንደሠራህ ይናገራል። ምናልባት በየዋህነት “ታዲያ ምን አለበት?” ተብሎ የሚታለፍ ሊመስል ይችላል። ግን ይህ ያስፈለገው ለምንድነው? ሄዶ ሄዶስ ምን ሊያስከትል ይችላል? የሚለው መታየት ይኖርበታል። ድሮ ስምንት ሰዓት ብቻ ይሠራ የነበረ ሰው አሁን 10 ሰዓት መሥራት ያስፈልገው ይሆናል። ድሮ 12 ከሆነ አሁን 14 ሰዓት ይፈጃል። 5ቀን ብቻ የሚሠራው አሁን ሳምንቱን ሙሉ ሠርቶ ላይበቃው ይችላል። ይህ በቤተሰብ ላይ ለሕብረተሰባችን በሚደረግ የበጎ አድራጎት ሼል ላይ ችግር ያመጣል። ገቢም ላይ የሚያሳድረው ጫና ይኖራል። የዲሲ መንግሥት ሕጎችን የሚያውቁው አንድ ታክሲ አሸከርካሪ 40 ሰዓትና አምስት ቀን ሰርቶ ከ25-30ሺ ዶላር በዓመት መሥራቱን ነው። ከዚያ በላይ የሚሠራ የበለጠ ሊያገኝ ይችላል። አሁን እንኳን ከዚያ የበለጠ ሊሠራ ለአብዛኞቹ ያለውንም ይዞ መቀጠል አሳሳቢ እየሆነ ይመስላል? ለውጡ ያስፈለገው ለምንድነው? ነገሩ ሲጀመር እንዲህ ነው። በ2011 “Modernization of taxi cab Industry “ ተባለ። የታክሲ አገልግሎትን ዘመናዊ ለማድረግ መሆኑ ነው። ለዚህ ሲባል አንዳንድ ደንቦች ወጡ። አንደኛ ክሬዲት ካርድ ማሽን መግጠም። ሁለተኛ ቀለም የታክሲ ቀለም አንድ ዓይነት እንዲሆን (ታክሲዎች አንድ ዓይነት እንዲቀቡ ማድረግ) ። ሶስተኛ ከታክሲው አናት ላይ የሚያበራ ምልክት (ዶም ላይት) እንዲገጠም። አምስተኛ ነዳጅ ቁጠባ ወይም አየር ብክለት መቋቋሚያ እንዲሆን በኤልክትሪክ የሚሠሩ (ሃይብሪድ) መኪኖች... እንዲሆኑ ተባለ። ደንብ በደንብ ላይ እየተነባበረ መጣ። ችግሩ ደንቡ መከበሩ አይደለም። ችግሩ የታክሲ አሰራር መሻሻሉ ሳይሆን ወጪው በሙሉ በታክሲ ነጂ ላይ እንዲጫን መሆን ብቻ ሳይሆን ታክሲ ነጂው በጥድፊያን በውድ እንዲገዛ 4 መደረጉ ነው ::ከዚህም በተጨማሪ ታክሲ ነጂው በ እየአንዳንዱ መንገደኛ 0,25 ሳንቲ እንዲከፍል ሲደረግ የሰራበትንም ገንዘብ ከ ጵጽጵ ዎች ተሰልፎ እንዲቀበል ተደርጓል:: ግን ክሪዴት ካርድ ማሽን ሲገጠም ማሽንኑን የሚገጥመው ማነው? ስንት ያስከፍላል? የባለታክሲው መብት እዚህ ላይ ምንድነው የሚለው ነው። ኩባንያዎችን ለመጥቀም ሲባል የማሽኑ ዋጋ ከተቆለለ ማን ይከፍላል? ለምንድነው ገበያው መወሰን ሲችል ከዚህ ኩባንያ ብቻ ግዙ የሚባለው? እዚህ ላይ ያልተቃወሙት አሠራር በጊዜ ሂደት ባለታክሲዎችን በወጪ እያደቀቀ ከገቢያ ያስወጣቸዋል። ነገ ይህን ዓይነት መኪና ብቻ ግዙ ፤ ስትግዙ ደግሞ ከዚህ ኩባንያ ብቻ ነው የምገዙት ማለትን ያመጣል። ያን የቻለ ሲገዛ ያልቻለ ከገበያ ይወጣል። ምክንያቱም ይህንን ችግር የዲሲ መንግሥት ያውቀዋል። በማወቁም ነው የክሬዲት ካርድ ማሽኑ ማስገጠሚያ ወጪ ሊበዛ ስለሚችል መጀመሪያ እኔ እከፍላለሁ ብሎ ነበር። ኋላ ደግሞ የለም እንዲያውም 35 ሚሊዮን ዶላር በጀት ልመድብና ሌላውን ባለታክሲዎች ይክፈሉ ተባለ። ባለታክሲዎች ከከፈሉ ደግሞ ምርጫ ይሰጣቸው ተባለ። መምረጥ የሚችሉት ግን ከነዚህ 8 ድርጅቶች ብቻ ነው ማሽኑን ግን በ100 ዶላር ይግዙት በማለት አስገደዱ። አንድ ሺ ምርጫ እያለን 8 ብቻ ለምን ይሆናል? ሌላ ስቴት ግን ይህ የለም። ለምሳሌ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ ያሉት ባለታክሲዎች ራሳቸው ሄደው መርጠው እንዲገዙ ነው ምርጫው የተሰጣቸው። ዲሲ ግን እንዲሠሩ ተፈቅዶላቸዋል። ይህ ሙስና ሊኖርበትም ቢችል ግልጽ አድልዎ ነው። ይህን በሚመለከት ክስ ተመስርቶ ጉዳዩ ጃንዋሪ 20 ይሰማል። የተፈራው ደረሰ?!ስሕት እንደ ትክክል ሲቆጠር :: ለዚሁ ሁሉ ችግሩ ሰዎች አይጠይቁም። አንብበው ከመረዳት ይልቅ በሰሙት የመነዳት ነገር አለ። መረጃውንም በጽሑፍ የሚያቀብል ወገን የለም። ሁሉም ነገር የሚንቀሳቀሰው በወሬና በስማበለው ነው። የሚያወሩትም ሰዎች ስለጉዳዩ በጥልቀት የሚያውቁ አይደሉም። በጉዳዩ የተካኑ ጉዳዩን ሥራዬ ብለው የያዙት አዋቂዎችን ከመስማት ሁሉም አዋቂ እየሆነ ነገሮችን ይምታታሉ። እንደ ፖለቲካው ሌላ የማያስፈልግ መልክ እየያዙ ለንትርክ ለሐሜትና ለጥርጣሬ በር ይከፍታሉ። “እንድ ሰው ዛሬ ተነስቶ እንደዚህ ሊደረግ ነው ሰው ሁሉ መኪናውን ቶሎ ቢሸጥ ያዋጣውል ብዬ ብናገር የሚያምነኝ ብዙ ሰው አላጣም። እንዴት? ለምን? ማን ያለው ብሎ መመርመር የሚወድ የለም። ይህም የራሱ አስተዋጽኦ አለው።” ብለዋል አቶ ዓለሜ። የተገጠሙ ማሽኖች ቶሎ ቶሎ መበላሸት ጀምሩ። የተበለሸውን ማሽን ለማሠራት ለዚህ ብቻ የተመደቡ ጋራዦች ከአቅማቸው በላይ እየሆነ ባለታክሲዎች መኪኖቻቸው ወስደው ጋራዥ ማቆም ጀምረዋል። አንዳንዴ ከ4-5 ሰዓት ታጠፋለህ። ጋራዦቹ በቂ እውቀት የሰለጠነ በቂ የሰው ኃይል የላቸውም። በዚያ ላይ ወጪው ቀላል አይደለም። በየእያንዳንዱ ጉዞ (ትሪፕ) 25 ሳንቲም ክፍሉ ማለቱም ሌላው መነጋገሪያ ነው። በዲሲ ታክሲ ኮሚሽነሩ አማካይነት ባለታክሲዎች ላይ ጦርነት የታወጀ ይመስል ያለቅጥ የተንዛዛው ቁጥጥርም አሳሳቢ ነገር ነው። ለምሳሌ አንድ ዓይነት ቀለም መቀባት ላይ ያለው አሠራር የሚገርም ነው። እኛ ላይ ጠበቅ ያለው ቁጥጥር ሌሎች ላይ አይሠራም። ለምሳሌ UBER X የተባለው የታክሲ ኩባንያ ያለ ቁጥጥር (without Regulations) እንዲሠራ ተፈቅዶለታል። እነሱ የተደራጀ አቅም ስላላቸው ቀለም የመቀባት ግዴታ የለባቸውም። ሌሎች ስቴቶች ቨርጂኒያም ሆነ ሜሪላንድ የተከለከሉ ከዚህ ለመውጣት ኢትዮጵያዊው ለመብቱ መታገል አለበት። ያ ደግሞ የመደራጀትን አቅም ይጠይቃል። ለዚህም ሲባል በርካቶች የአሜሪካ ሠራተኛ ማህበር (Teamsters ) ውስጥ ገብተዋል። እዚያ መግባቱ ብቻውን ግን በቂ አይደለም። ተገቢውን ወርሃዊ ክፍያ መክፈል ይገባል። ያ ባለመሆኑ ከድርጅቱ የተፈለገውን እርዳታና አቅም ማግኝት አልተቻለም። በዋሽንግተን ዲሲ ፖለቲካው ውስጥም ገብቶ ተጽእኖ ለማሳረፍ ትልቁ ችግር አብዛኛው ታክሲ አሽከርካሪ የሚኖረው ዲሲ ሳይሆን ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ውስጥ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ዲሲም ውስጥ ቢሆን ኢትዮጵያውያን ያላቸው ጉልበት ከሚያውቁት በላይ መሆኑን የሚገልጹ አሉ። ምንም እንኳን ቲምስተር ለመርዳት አቅሙ ኖሮት ፈቃደኛ ቢሆንም ጉዳዩን ታክሲ የሚነዳ ብቻ የሚያውቀው በመሆኑ ቲምስተርን መገፋፋት ተገቢ ነው::በሜሪላንድ እና ቨርጂኒያ የአሉት ሴናተሮች ኮንግረስ ተመራጫጮች ጉዳያችንን እንዲያዩ ማደረግ ሲገባቸው ቲምስተር እስከ አሁን ለምን ይህንን እንዳላደረገ መጠየቅ ተገቢ ነው:: “አዋቂዎችን የማፍራት እነሱን የመከተል ልምድ ሊኖረን ይገባል። መኪናችን ሲበላሽ መካኒክ ጋ ወስደን እናሰራለን መብታችን ሲበላሽ ግን እኛ አዋቂዎች የምንሆነው ለምንድነው? መብታችንን ይበልጥ ማስከበር የምንችለው ጉዳዩን ወደ ሥራዬ ብለው ወደ ተከታተሉትና ወደ ወደ ገጽ 10 ሚያዉቁት ሰዎች ስንወስድ ነው። በንግድ ሚኒስቴር ሼር እንዲተዳደር በመንግሥት የተቋቋመው “አለ” የተባለው የኢትዮጵያ ጅምላ ንግድ ድርጅት፣ አትራፊ ሆኖ በግል ኩባንያነት ይተዳደራል። በስም ጅምላ ይሁን እንጂ በቸርቻሪ ሱፐር ማርኬት ገበያነትም ይንቀሳቀሳል። የአንድ ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል አለው። ሁሉንም የምርት ዓይነቶች ገበያው ውስጥ ለማገበያየት የተነሳ ነው። የጅምላ ንግድ ድርጅቱ “አለ” ሠራተኞቹን በተለይም ማኔጅመነቱን ከአገር ውስጥና ከውጭ እየቀጠረ ነው። ኢትዮጵያው ውስጥ እንደ ዎል ማርት ዓይነት የገበያ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሉ የሸቀጥ አቅራቢዎች ጋር እየተነጋገረ ነው። ሸቀጦቹ ለሆቴሎች፣ ለግሮሰሪዎች፣ ለኪዮስኮች፣ ለባርና ሬስቶራንቶች ከገጽ 3 ይከፋፈላሉ። ከምርቶቹ መካከል የሸቀጣ ሸቀጥ፣ የተለያዩ መጠጦች፣ የታሸጉ ምግቦች፣ የውበትና የግል ንጽህና መጠበቂያ፣ የጽህፈት መሳሪያዎችና የሌሎች ምርቶች ይገኙበታል። እነዚህን ሸቀጦችን እያስመጡ የሚሸጡ ድርጅቶች ከአሁን በኋላ መንግሥት ከአቋቋመው የጅምላ መደብር እንዲገዙ ይደረጋል። ተጠቃሚዎች ደግሞ ከድርጅቱ ወይም ከአከፋፋዮቹ ይገዛሉ። በአዲስ አበባ ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ሦስት የጅምላ መሸጫ መደብሮች በኤፕሪል 2014 ፣ በመርካቶ በቃሊቲ እና መገናኛ አካባቢ ይከፈታሉ።ከዚያም በሌሎች 26 ከተሞችም 37 አከፋፋይና የችርቻሮ መደብሮችና ትላልቅ መጋዘኖች እንደሚኖሩት ተነግሯል። እየተባባሰ የመጣውን የዋጋ መናር ለመቆጣጠርና ከንግዱ ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ገቢ ከፍ ለማድረግ ሌላ አማራጭ ተደርጎ መወሰዱም ተገልጿል። ከነጻ ገበያው ጋር ፍጹም ተጻጻሪና የመንግሥትን ሁሉን ነገር የመቆጣጠር ፍላጎት ተደርጎ መታየቱም አልቀረም። ስብሐት ግንዛቤ አግኝቷል። (TPLF) ህወሃት ሰው ወደደም አልወደደም መለሾ ከነበረበት በጣም የጠነከረ ድርጅት ይሆናል። አሁን እንኳ ከነጥንካሬው ነው ያለው። የጥንካሬው ዲግሪ መለሾ ከነበረበት በላይ ጠንክሮ ይወጣል። ሰው ይወደዋል ወይ አይወደውም አይደለም። የትግራይ ህዝብ ግን ወደዚህ ደረጃ ይደርሳል። ሳቅ አቋረጣቸው አንድ ድርጅት የበለጠ ከሆነ ያ... ዘኢትዮጵያ - የመለስ ራዕይ ይባላል አሁን ለምሳሌ ። ሁለት አየር ላይ ያሉ ነገሮች አሉ። አንዱ ወገን አቶ መለሾ ህወሓትን ገድለውት ነው የሄዱት። ይህንን አስተሳሰብ እንዲያውም እነ አቦይ ስብሐት የሚጋሩት ነው፣ የሚቆጩበት ነው፣ የሚል አለ ። በሌላ በኩል ደግሞ የለም መለሾ ገድሎት ሳይሆን እንዲያውም አጠናክሮት ነው የሄደው የሚሉ ወገኖች አሉ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው? ዘኢትዮጵያ - አቶ መለሾ አምባገነን ነበሩ እየተባለ የሚሰጥ አስተያየትም ስላለ ነው። ሥልጣን በተለይ ከፍፍሉ ወይም እነዚያ ሰዎች ከተባረሩ በኋላ መለሾ... አቶ ስብሐት- እኔ አሁን እንደዚህ እንትን ስለሆን አንድ ላይ ስለሌለን አስቸጋሪ ሊሆን ነው........ አንድ ድርጅት አንድነትንም ይሁን አረናም ይሁን እንደ ድርጅትነቱ ይወለዳል ይሞታል ይለወጣል ይሻሻላል። TPLF ከመለስ በኋላ የሚቀጥል አለው የሚቀጥሉ ጸጋዎች አሉ የሚሻሻሉ አሉ፣ የሚለወጡ አሉ። ስለዚህ ይሄ ኢተርናል ነው። ይሄ የሚሻሻል አለ፣ የሚቀጥል አለ፣ የሚለወጥ አለ። አሁን በፕሮግራም የሚለወጥ ነገር የለም። ያው ካፒታሊዝም ካፒታሊዝም ነው። ካፒታሊዝሙ ደግሞ ደቨሎፕመንታል ነጻ አገራዊ ኢኮኖሚ ነው። ስለዚህ መለሾ ድርጅቱን ገድሎት አልሄደም። እንደማንኛውም ድርጅት አባይ ስዬ ሄደ ትቶት የሚሄድ የሚሻሻል ነው የሚለውጥ ነው የሚቀጥል ነው ዳይናሚካሊ እንደሱ እያለ ይሄዳል። እና መለሾ ድርጅቱን አልገደለውም። በህይወቱ ነው ያለው ግን ይጠነክራል። አቶ ስብሐት- ሼል ሁልጊዜ ኮምፔሌክስ እየሆነ ይሄዳል አይደለም? አሁን ማስፋቱ በጣም አስፈላጊ ነው። It is very important! ሁለት ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትሮች አደረገ። ሁለት ነው ሶስት? ዘኢትዮጵያ - ግን የሳቸው አመራር ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ ማርያም ወደ ስልጣን ሲመጡ “አሁን የቡድን አመራር (ኮሌክቲቭ ሊደርሺፕ) ነው ያለው” ብለው ነበር። አሁን ነው ብለው ያሉት። ከአቶ መለሾ ሞት በኋላ። ምን ማለት ነው ? ያ ቡድን አመራር ማለት? አሁን የጋራ አመራር አለ ብለው ያምናሉ? በፊትስ አልነበረም ብለው ያምናሉ? አቶ ስብሐት- እኔ አቶ ኃ/ ማርያም ይሄን ቢመልሰው ነው ጥሩ የሚሆነው። ዘኢትዮጵያ ግን ልክ - አባባሉ አይደለም? አቶ ስብሐት- የአቶ ኃ/ማርያም አባባል ከየት እንደተነሳ ወደ ግጭት መሄድ አልፈልግም። ምን ማለቱ እንደሆነ። ድሮ የጋራ አመራር አልነበረም ማለቱ ነው ልል አልችልም። ነበረ ማለቱ ነው ልልም አልችልም። ከኃይለማርያም አልነሳም። ድርጅቱ ከነበረው የጋር አመራር የበለጠ የጋራ አመራር አግኝቷል አሁን። ድሮም ባህርይው የጋራ ነው። ዘኢትዮጵያ የበለጠ - ለምንድነው ያገኘው? አቶ ስብሐት- ሳቅ...ሁል ጊዜ ምን አልኩህ አንድ ድርጅት...አሁን ዘኢትዮጵያ - ገባኝ ግን... አቶ ስብሐት- አይደለም። የበለጠ ካልኩህ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ ነው። ድሮም የጋራ አመራር ነበር። አሁን እሱ አሰፋው። ማስፋቱ የጋራ አመራሩ ማስፋቱ ስለተገኘ ነው። ማሻሻል.. አቶ ስብሐት- ይቺ ድገማት አሁን ይቺ ድገማት? ድሮም የጋር አመራር ነበረ። አሁን ደግሞ የጋራ አመራሩን ማስፋት አስፈለገ። ዘኢትዮጵያ - ለምን ማስፋት አስፈለገ አሁን የጋራ አመራሩን? ዘኢትዮጵያ - ሶስት ነው አቶ ስብሐት- አራት ከፍተኛ ባለሥጣኖች ደግሞ አድቫይዘርስ ብሎ አስቀመጠ። በረከት አባይ.. ዘኢትዮጵያ - ካሱና ኩማ አቶ ስብሐት- አዎ አስፈላጊ ሆኖ አገኘዋ! ልሰራ ይሄ ያስፈልገኛል አለ። ይሄ ትክክል ይመስለኛል። ድሮም የጋራ አመራር ነበረ። አሁንም ደግሞ ያ የጋራ አመራሩ አሰፋው። ለምን ይሄ ነው የሚቀለኝ በዚህ ነው የተሰጠኝን ሼል ልፈጽም የምችለው አለ። ዘኢትዮጵያ - የመለስ ራዕይ ይባላል፣ የኢህአዴግ ራዕይ፣ የመለስ ራዕይ ምን ማለት ነው? መለሾ የራሳቸው ራዕይ ነበራቸው? በድርጅቱ ውስጥ? የመለስን ራዕይ ለማስፈጸም ይላሉ ከኃ/ ማርያም ጀምሮ ሁሉም የድርጅቱ አመራር አባላት እርስዎ ማለትዎን አላስታውስም ግን ምንድነው የሚመስልዎት? አቶ ስብሐት- የኢህአዴግ ራዕይ ነው። መለሾ ይህንን ራዕይ እውን እንዲያደርግ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ፋክቱን ነው የምነግርህ ራዕዩ የኢህአዴግ ነው በዚህ ራዕይ መለሾ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዘኢትዮጵያ - የአቶ መለሾ ጠንካራ ጎኖች ብዙ ተብሎላቸዋል፣ ደካማ ጎናቸው ምንድነው? አቶ ስብሐት- ደካማ ጎኑ ብዙ ጎልቶ የሚታይ (Noticable) አይደለም። ጠንካራ ጎኑ የጎላ (dominant) ነው። ዘኢትዮጵያ - እርስዎ ምንም ቅሬት አልነበረትዎም በድርጅቱ አካሄድ ከውጭ ሆነው በሚያዩት? አቶ ስብሐት- ብዙ የሀሳብ ልዩነት ነበረ። በጣም! በጣም ብዙ የሀሳብ ልዩነት ነበረ። ዘኢትዮጵያ - ለምሳሌ ምንድነው ከነበሩት የሀሳብ ልዩነቶች በጣም ትልቁ ነው የሚሉት? የጎላው ምንድነበረ? ወደ ገጽ 6