SlideShare une entreprise Scribd logo
1  sur  41
ግዴታዬን እወጣለሁ መብቴን እጠይቃለሁ!
ማህሌት አምዴ ጥቅምት/2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የታክስ ምንነትና ከግብር ከፋዮች
የሚጠበቅ ኃላፊነት
ከህግ ተገዢነትና ታክስ አስተዳደር አንፃር
ለሰራተኞች የተዘጋጀ
2
የሰነዱ ይዘት
01 መግቢያ
02 የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እና ጠቅላላ መረጃ
03 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ ኃላፊነት
3
•
ክፍል አንድ - መግቢያ
• አጠቃላይ የታክስ አስተዳደር መርህ ላይ ግልጽነትን ለመፍጠር ፤
• የህግ ተገዢነት በተጨባጭ ከታክስ ኦፕሬሽን አንፃር ምን ይመስላል የሚለውን ግንዛቤ
ለማስጨበጥ፤
• ህጉን ተረድቶ የሚመለከታቸው አካላት ግዴታቸውንና ኃላፊነታቸውን በቀላሉ እንዲወጡ
ለማስቻል፤
የሥልጠናው ዓላማ እና የገቢ ሰብሣቢ ተቋማት ዓላማ
• ከግብር/ታክስ/ እና ከተለያዩ ቀረጦች የሚገኝ የመንግስት ገቢን መሰብሰብ፣
• ሕጋዊ የሆነውን የንግድ እንቅስቃሴን ማሣለጥ፣
• የማህበረሰቡን ደህንነት መጠበቅ እና
• ፍትሐዊ የሐብት ክፍፍል እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡
የሥልጠናው ዓላማ
የገቢ ሰብሣቢ ተቋማት
በዋነኝነት
የመቋቋማቸው ዓላማ
4
• ገቢ ባገኘ ሰው ላይ ብቻ ግብር መጣል (tax only income) ፤ በጣም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ከግብር ነጻ
ማድረግ ፤ ገቢው እያደገ ሲሄድ እየጨመረ በሚሄድ የግብር ማስከፈያ መጣኔ ግብር ማስከፈል
(progressivity/
ዋና የታክስ አስተዳደር መርሆች/Principles of taxation/ - የታክስ አጣጣልንና የታክስ ህግና ሥርዓት አወቃቀርን
በተመለከተ ምን ሁኔታዎችን ማሟላት እንዳለበት ከሞላ ጐደል በዓለም ላይ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት
ያገኙ የታክስ ህግና ሥርዓት መሠረቶች የታክስ መሠረታዊ መርሆዎች በመባል ይታወቃሉ
• ለአንድ ዓይነት ግብር አንድ ዓይነት የግብር መጣኔ መጠቀም ፤ወጥ በሆነ የማስከፈያ መጣኔ ግብር
ማስከፈል ፤ ከገቢው መጠን ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የግብር መጠን ማስከፈል (proportionality of tax
to income)
• በሁሉም ግብር ከፋዮች ላይ የሚያርፈው የግብር ጫና እኩል ወይም ተመጣጣኝ እንዲሆን ማድረግ
(proportional equality of tax burden) ፤ግብር የመክፈል አቅም ያለው ሁሉ እንደየአቅሙ ግብር
እንዲከፍል ማድረግ (equitable contribution to the national revenue)፤በግብር ምንም ዓይነት
ልዩነት አለማድርግ (tax without discrimination)፤
• መሰረታዊ የታክስ ህግ መርሆዎችና ደንቦች በአዋጅ መደንገግና ለረጅም ጊዜ ቋሚ ሆነው የሚቀጥሉ
መሆን አለባቸው ፤ መለስተኛ ክብደት ያላቸው ጉዳዮች ደግሞ በመለስተኛ ህጎች (regulations)
መደንገግ አለባቸው፡ ለመመሪያና ለባለስልጣን ውሳኔ የሚተው ጉዳዮች የግብር ከፋዮን መሰረታዊ
መብቶች የማይነኩና አነስተኛ ሥነ ሥርዓታዊ ጉዳዮች ብቻ መሆን አለባቸው፡፡
ክፍል ሁለት
የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እና ጠቅላላ መረጃ
የመክፈል አቅም
(Ability to pay)
ተመጣጣኝነት
(fairness)
ፍትሃዊነት
(equitability)
ተገማችነት
(predictability)
5
• ህጉ ተቃርኖ የማይታይበትና ከዳር እስከዳር የሚጣጣምና ወጥ መሆን አለበት፡
• በተፃፈ ህግ የሚመራ እና ለድርድር ክፍት ያልሆነ መሆን አለበት፡
ዋና የታክስ አስተዳደር መርሆች…
• አቅም በፈቀደ መልኩ የታክስ አስተዳደር እና የታክስ ህግ ተገዢነት ወጪ በጣም አነስተኛ እና በአጭር
ጊዜ የሚከወን መሆን አለበት፡
• ህጉ ለግብር ከፋዩ ጭምር ግልጽና ለመረዳት የሚያመች እንዲሁም ለአሰራር ቀላል መሆን አለበት፡
• የታክስ ስርዓቱ ተጨማሪ ኢንቨስትመንትን /የንግድ ስራ እንቅስቃሴን/ የሚገታ መሆን የለበትም
የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እናጠቅላላ መረጃ የቀጠለ…
ወጥነት
(consistency)
በቅልጥፍና /በብቃት
(Efficiency
principle)
ግልጽነትና አመቺነት
(clarity simplicity)
ኢንቨስትመንትን
የሚያበረታታ
(Investment or
productivity
Principle)
6
•
የቀጠለ…
አጠቃላይ መረጃ
• ሕግ የሰውን ልጅ ባህሪ፣ እንቅስቃሴና ግንኙነት መልክና ሥርዓት ለማስያዝ ፖለቲካዊ
አደረጃጀት ባለው ህብረተሰብ ውስጥ ስልታዊ በሆነ መልኩ ኃይል መጠቀምን የሚፈቅድ
ሥርዓት ነው፡፡
• የፍርድና የአስተዳደር ውሳኔዎች ፍሰት፣ህጋዊ እርምጃዎችና የህግ ውሳኔ ሂደቶችን
የያዘ ነው፣
የታክስ አስተዳደር በተፃፈ ህግ ከላይ የተመለከቱትን መርሆች ተከትሎ እንዲመራ የሚጠበቅ ስርዓት ነው
• የታክስ ህግ መንግስት (state) ሰዎች ወይም ድርጅቶች የሚከፍሉትን የታክስ
ዓይነት፣የማስከፈያ ምጣኔ፣የታክስ አወሳሰኑን፣አሰባሰቡን በአጠቃላይ ታክስ
የመክፈል ግዴታንና የግዴታቸውን አፈፃፀም አስመልክቶ አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ
በጽሁፍ የሚያውጀው የታክስ አስተዳደርና የአሠራር ሥርዓቱ መሠረታዊ
መርሆዎች የሚገለጹበት የህግ ሰነድ ነው፡፡
የህግ ምንነት
የታክስ ህግ ምንነት
7
አጠቃላይ መረጃ …
ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣን (taxing power)
• ከታክስ የሚሰበሰብ ገቢ ለአንድ መንግስት ህልውና እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ ታክስ የመጣልና የማስከፈል
ሥልጣን ለመንግስት ብቻ የተሰጠ ሥልጣን ነው፡፡ ለግለሰብ ወይም ለሌላ አካል የዚህ ዓይነት ሥልጣን
በየትኛውም ዓለም አልተሰጠም፡፡
• በኢትዮጵያ መንግስት (state) ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣኑን የሚያገኘው ከህገ መንግስቱ አንቀጽ
96፣97፣ 98 እና 99 ነው፡፡
• የህገ መንግስቱ አንቀጽ 96 የፌደራል መንግስትን መሠረታዊ የታክስና የግብር ሥልጣን የሚደነግግ ሲሆን
• አንቀጽ 97 የክልል መንግስታት የታክስ አስተዳዳር ስልጣንን ያሣያል
• አንቀጽ 98 ደግሞ የክልልና የፌደራል መንግስታት የጋራ የታክስና የግብር ሥልጣንን ይወስናል፡፡ አንቀጽ 99
በህግ በግልጽ ለፌደራል መንግስት ወይም ለክልል መንግስታት ወይም ለሁለቱም በጋራ ያልተሰጠ የታክስና
የግብር ሥልጣን በፌዴሬሽንና በህዝብ ተወካዮች ምከር ቤቶች የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምጽ
የታክስ ሥልጣኑ ለፌደራል መንግስት፣ ለክልሎች ወይም ለሁለቱም የጋራ ሥልጣን እንዲሆን ይወስናል፡፡
8
• የታክስ ሥርዓት የምንለው የታክስ ህጉንና ይህን የታክስ ህግ መሠረት በማድረግ በየደረጃው
የሚወጡ መመሪያዎችና የአሠራር ሥርዓቶች በታክስ ባለሥልጣኑ የሚዘረጉ የታክስ አወሳሰንና
አሰባሰብ፣ የኦዲት ሥርዓቱንና የመረጃ አስተዳደር ሥርዓቱን ጨምሮ የአገልግሎት አሰጣጡንና
የቅሬት አፈታት ሥርዓቱን በማጠቃለል “የታክስ አስተዳደር ሥርዓት” ብለን የምንጠራውን
አስተዳደራዊ ሥርዓት የሚወክል መሠረታዊ ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡
የታክስ ሥርዓት ምንነት
 ግሎባል (aggregated) የታክስ ሥርዓት
 ስኬጁላር (disaggregated) የታክስ ሥርዓት ተብለው የሚታወቁ ናቸው፡፡
• ግሎባል የታክስ ሥርዓት - ግብር ከፋዩ የሚያገኘውን ማንኛውንም ዓይነት ገቢ በአንድ ላይ በመደመር በአንድ
የግብር ማስከፈያ ምጣኔ ግብር እንዲከፍል የሚደረግበት ሥርዓት ነው፡
• ስኬጁላር የታክስ ሥርዓት የሚባለው አንድ ግብር ከፋይ የሚያገኛቸውን ገቢዎች እንደየገቢው ዓይነት
በመከፋፈል ወይም በመመደብ ለእያንዳንዱ የገቢ ዓይነት በስኬጁል የተቀመጡ የግብር ማስከፈያ
ምጣኔዎችን በመጠቀም የተለያየ ግብር በመወሰን የተለያዩ የህግ መርሆዎችንና መሪ ድንጋጌዎች
ተጠቅሞ ታክሱን የሚሰበስብበት ሥርዓት ነው፡፡
• የኢትዮጵያ የታክስ ሥርዓት ይህንን ዓይነት የታክስ ሥርዓት የሚከተል ነው
አጠቃላይ መረጃ …
የታክስ ሥርዓት
የታክስ ሥርዓት
ዓይነቶች/Types of
Taxing System/
ግሎባል (aggregated)
የታክስ ሥርዓት
ስኬጁላር
(disaggregated)
የታክስ ሥርዓት
9
አጠቃላይ መረጃ …
 የገቢ ሠንጠረዦች(Schedules of Income) /አንቀጽ 8/
• በገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 አምስት የግብር ሠንጠረዦች ይፋ ተደርገዋል፡-
ሠንጠረዥ ሀ - ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ (income from employment)
ሠንጠረዥ ለ - ከቤት ኪራይ የሚገኝ ገቢ (income from rental of building)
ሠንጠዥ ሐ - ከንግድ ሥራ የሚገኝ ገቢ (income from Business)
ሠንጠረዥ መ- ሌሎች ገቢዎች (other income)
ሠንጠረዥ ሠ - ከግብር ነፃ የሆኑ ገቢዎች (exempt income)
• በአንድ ሠንጠረዥ ውስጥ የሚወድቁ የተለያዩ ገቢዎችን ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ያገኘ ሰው
ሁሉም ገቢዎች ተጣምረው በዚያው ሠንጠረዥ ሥር ግብር ይከፈልባቸዋል፡፡
10
አጠቃላይ መረጃ …
 የተፈፃሚነት ወሰን /አንቀጽ 7/
የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 የህግ አንቀጽ የተደነገገው የኢትዮጵያ መንግስት ያለውንና ሊኖረው
የሚገባውን የግብር ሥልጣን (Tax jurisdiction) መሠረት በማድረግ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት አዋጁ
- የኢትዮጵያ ነዋሪ በሆኑ ሰዎች ላይ በዓለም ዙሪያ በሚያገኙት ገቢ ላይ ግብር እንዲከፍሉ፣
- የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆኑት ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ባገኙት ገቢ ላይ ወይም የኢትዮጵያ ምንጭ
በሆነ ገቢ ላይ ብቻ ግብር እንዲከፍሉ ደንግጓል፡፡
11
•
አጠቃላይ መረጃ …
የሚከተሉት የኢትዮጵያ ነዋሪዎች ናቸው፡-
- ነዋሪ የሆነ ግለሰብ
 ኢትዮጵያ ውስጥ ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ (domicile) ያለው፣
 በመንግስት ተመድቦ በውጭ አገር የሚሠራ ኢትዮጵያዊ ዜጋ፣
 በኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በተከታታይ ሳያቋርጥ ወይም በመመላለስ ከ183 ቀናት በላይ የኖረ
ግለሰብ፣
- ነዋሪ የሆነ ድርጅት
 ኢትዮጵያ ውስጥ የተቋቋመ /የተመሠረተ/፣
 ወሳኝ የሆነ የሥራ አመራር የሚሰጥበት ሥፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው፣
የፌደራል መንግስት፣ የክልል መንግስታትና ከተማ አስተዳደሮች፣
የተፈፃሚነት ወሰን
የሚከተሉት ገቢዎች ከኢትዮጵያ የመነጩ ናቸው፡
• በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከናወን የቅጥር አገልግሎት የተገኘ ገቢ
- ክፍያው የሚፈፀምበት ሥፍራ የትም ቢሆን፣
- ውሉ የተፈረመው የትም ቢሆን፣
- የአሠሪው ነዋሪነት የትም ቢሆን፣
- ሠራተኛው የኢትዮጵያ ነዋሪ ቢሆንም ባይሆንም፣
• በኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት፣በክልል መንግስታት ወይም በከተማ አስተዳደሮችና በእነዚህ ስም ለቀጣሪው የተፈፀመ ክፍያ
- የቅጥር አገልግሎቱ የትም ቢከናወን፣
• በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያገኘው የግድ ሥራ ገቢ፣
ነዋሪነት
የገቢ ግብር
አዋጅ
979/2008
አንቀጽ 5
የገቢ
ምንጭ
የገቢ ግብር አዋጅ
979/2008
አንቀጽ 6
12
•
የተፈፃሚነት ወሰን…
- በቋሚነት በሚሠራ ድርጅት አማካኝነት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራ የሚያገኘው ገቢ፣
- በቋሚነት የሚሠራው ድርጅት ከሚያስተላልፏቸው ዕቃዎች ወይም ሸቀጦች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሣሣይ የሆኑ
ዕቃዎችን ወይም ሸቀጦችን ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጥታ በማስተላለፍ የሚያገኘው ገቢ፣
- በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት ከሚያከናውናቸው ማናቸውም የንግድ ሥራዎች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሣሣይ የሆኑ
ሌሎች የንግድ ሥራ እንቅስቃሴዎችን ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጥታ በማከናወን የሚያገኘው ገቢ፣
የገቢ ምንጭ…
- በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ድርጅት የሚከፍለው የትርፍ ድርሻ፣
- የማይንቀሳቀስ ሃብትና በኢትዮጵያ የሚገኝን የሚንቀሳቀስ ሃብት በማከራየት የሚገኝ ገቢ፣
- በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝን የማይንቀሳቀስ ሃብት በማስተላለፍ ወይም ግንኙነት ባላቸው ሰዎች የተያዘንና ከዋጋው 5ዐ%
በላይ የሆነን የማይንቀሳቀስ ሃብት ጥቅም በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ፣
- በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ኩባንያ ያወጣው (የሚሸጠው) አክሲዮን ወይም ቦንድ፣
- በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኝ መድን ለተገባለት የአደጋ ሥጋት የሚከፈል የመድን አርቦን፣
- በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከናወን የመዝናኛ ወይም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚገኝ ገቢ፣
- በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄድን የዕድል ሙከራ በማሸነፍ የሚገኝ ገቢ፣
- የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው የኢትዮጵያ ነዋሪ ከሆነ ሰው የሚያገኘው የወለድ ገቢ፣
- የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው የኢትዮጵያ ነዋሪ ከሆነ ሰው የሚያገኘው የሮያልቲ ክፍያ ገቢ፣
- የኢትዮጵያ ነዋሪ ለሌላ የኢትዮጵያ ነዋሪ የሚከፍለው የወለድ እና የሮያልቲ ክፍያ ገቢ፣
- የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት የኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው
የሚከፍሉት የሥራ አመራር ወይም የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ፣
ኢትዮጵያ
ውስጥ ነዋሪ
ያልሆነ ሰው፣
የሚከተሉት
ገቢዎች
ኢትዬጽያ
ውስጥ
የመነጩ
ገቢዎች
ይባላሉ
/አ6 ንአ 4/
13
ክፍል ሶስት
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ ሚና /ኃላፊነት/
•በየትኛውም የታክስ አስተዳደር ስርዓት የግብር ከፋዮች
መሰረታዊ ግዴታዎች በ 4 ዋና ዋና ነጥቦች ይለካሉ፡-
1. ለግብር ከፋይነት መመዝገብ (Register):- የጣት አሻራ መስጠት፣ መለያ
ቁጥር ማውጣት፣ ለተ.እ.ታ መመዝገብ፤ ለኤክሳይዝ ታክስ ፤እና ልዩ ልዩ
ለውጦችን ማስታወቅ፤
2. ማስታወቅ (Filing):- የሥራ ግብር፣ የቤት ኪራይ ገቢ፣ የትርፍ ግብር
፣የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የኤክሳይዝ ታክስ ወ.ዘ.ተ ማሣወቂያዎች በተቀመጠው
ጊዜ ውስጥ ማስታወቅ፤
3. ሪፖርት ማድረግ (Reporting):- ትክክለኛ መረጃ /ከዲክላሬሽን ጋር በተያያዘ
የመስጠት ግዴታ፤
4. ታክስ/ግብር መክፈል (Payment):- የታክስ/ግብር ግዴታዎችን በፈቃደኝነት
በትክክለኛው መንገድ የመወጣት ሁኔታና በትክክለኛው ሰዓት በወቅቱ መክፈል፤
14
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ስለምዝገባ (የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀጽ 9
- 11)
ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ
•አስቀድሞ የተመዘገበ ካልሆነ በስተቀር በታክስ ሕግ መሠረት
ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ሰው በባለሥልጣኑ ዘንድ
ለመመዝገብ ማመልከት አለበት፡፡
•ነገር ግን ይህ ድንጋጌ፡-
በኢትዮጵያ የሚያገኘው ገቢ ብቻ በገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ 51 መሰረት በኢትዬጲያ ነዋሪ
ያልሆነ ሰው የትርፍ ድርሻ፣ ሮያሊቲ፣ ወለድ፣ የስራ አመራር ክፍያ ፣ የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ
ወይም የመድን አረቦን ከኢትዬጲያ ውስጥ ያገኘን ሰው እና አንቀጽ 53 መሰረት በኢትዬጲያ
ነዋሪ ያልሆኑ የመዝናኛ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም እንዲሁም
በሠንጠረዠ “መ” መሰረት የሚጣለው የመጨረሻ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ብቻ ያለው ግለሰብ
ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
15
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ …
ለምዝገባ - ባለሥልጣኑ ባጸደቀው ቅጽ መሠረት ማመልከቻ መቅረብ ይኖርበታል፡-
“የጸደቀ ቅጽ” ማለት በዚህ አዋጅ አንቀጽ 79 የተሰጠው ትርጉም ይኖረዋል፤ የአዋጁን አንቀጽ 79 ስንመለከት፡
በታክስ ከፋይ የሚቀርብ ማንኛውም የታክስ ማስታወቂያ፣ ማመልከቻ፣ ማስታወቂያ፣መግለጫ ወይም ሌላ
ሰነድ በፀደቀው ቅጽ መሠረት እንደቀረበ የሚቆጠረው ሰነዱ፡-
የሰነዱ ዓይነት በባለሥልጣኑ በፀደቀ ቅጽ መሠረት የቀረበ፣
ማንኛውንም ተያያዥ ሰነዶች ጨምሮ ቅጹ የሚጠይቀውን መረጃ የያዘ፣ እና
ቅጹ በሚጠይቀው መሠረት የተፈረመ፣ ሲሆን ነው፡፡
• የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ በሚወሰነው መሠረት የጣት አሻራ መለያን ጨምሮ የግለሰቡን
ማንነት ከሚያረጋግጥ የሰነድ ማስረጃ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፤ በፌደራል የታክስ አስተዳደር ደንብ
ቁጥር 407/2009 አንቀጽ 4 መሰረት ከሚከተሉት አንዱን የማንነት የሰነድ ማስረጃ ከሚያቀርበው
ማመልከቻ ጋር ያቀርባል፡- ወቅታዊ የግለሰቡ የነዋሪነት መታወቂያ ወይም የኢትዬጽያ/የሌላ ሀገር/ ፖስፖርት
ገጽ የተረጋገጠ ቅጂ ወይም ፣ የመንጃ ፈቃድ ቅጂ፣ ወይም የግለሰቡ የተረጋገጠ የልደት የምስክር ወረቀት ቅጂ
ወይም ባለስልጣኑ አስፈላጊ መስሎ የሚታየውን ሌላ ማንኛውንም ማስረጃ እንዲያቀርብለት ሊጠይቀው
ይችላል፡፡ ኩባንያ በሚሆንበት ጊዜ ኩባንያው የተቋቋመበትን ወይም የተመዘገበበትን የምስክር ወረቀት
ከማመልከቻው ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡
• ታክስ ከፋዩ ለታክስ የመመዝገብ ግዴታ ካለበት ቀን አንስቶ በ21 ቀናት ውስጥ ወይም ባለሥልጣኑ በፈቀደው
ተጨማሪ ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፡፡
• ባለሥልጣኑ ለመመዝገብ ያመለከተው ሰው በታክስ ሕግ መሠረት ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት
መሆኑን ሲያምንበት ይመዘግበዋል፤ የምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ ይሰጠዋል፡፡
16
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ …
• ነገር ግን አንድ ሰው ለመመዝገብ ሲያመለክት ያቀረበውን ማስረጃ ይህ ሰው ተጨማሪ የምዝገባ
ማመልከቻ ቅጽ ማቅረብ ሳያስፈልገው ባለሥልጣኑ ማስረጃውን ይህ ሰው በሌላ የታክስ ሕግ
ለአንድ የተለየ ታክስ እንዲመዘገብ ያለበትን ግዴታ ወይም ለመመዝገብ የተሰጠውን ፈቃድ
ለማሟላት ሊጠቀምበት ይችላል፡
• ይህ ቢኖርም ባለሥልጣኑ የአንድን ሰው ተጨማሪ ምዝገባ በተሟላ ሁኔታ ለማከናወን
የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ሌላ ተጨማሪ መረጃ ያቀርብ ዘንድ ይህንን ሰው ሊጠይቀው
ይችላል፡
• መመዝገብ ሲኖርበት ያልተመዘገበን ሰው ባለሥልጣኑ በፀደቀው ቅጽ መሠረት መዝግቦ የምዝገባ
የምስክር ወረቀት ሊሰጠው ይችላል፡፡
• የአንድ ሰው ምዝገባ ተፈፃሚ የሚሆነው የዚህን ሰው ምዝገባ በሚያረጋግጠው የምስክር ወረቀት
ላይ ከተመለከተው ቀን ጀምሮ ነው፡፡
• በአዋጁ መሰረት መመዝገብ ሲገባው ያልተመዘገበ እንደሆነ መመዝገብ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ
እስከተመዘገበበት ጊዜ ታሣቢ ተደርጐ በአዋጁ አንቀጽ 101 ፡-
• በታክስ ከፋይነት ያልተመዘገበ እንደሆነ የግብሩን 25% መቀጮ ይቀጣል፡፡
• የሚከፈል ግብር ከሌለ በየወሩ 1,000 ብር ይቀጣል
17
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ምዝገባን ስለመሰረዝ
• እንዲሰረዝለት ለባለስልጣኑ ማመልከት አለበት፣
• ምዝገባን ለማሰረዝ የሚቀርበው ማመልከቻ በፀደቀው ቅጽ መሠረት፣ እና የተመዘገበው ሰው በሁሉም
የታክስ ሕጐች የተጣለበት የመመዝገብ ግዴታ ከተቋረጠበት ቀን አንስቶ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ወይም
ባለሥልጣኑ በሚሰጠው ተጨማሪ ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፡፡
• አንድ ሰው በዚህ መሰረት ለመሰረዝ ማመልከቻ ካቀረበ በሌላ የታክስ ሕግ ለአንድ የተለየ ታክስ የተደረገው
ምዝገባ እንዲሰረዝለት ጭምር እንዳመለከተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
• አንድ ሰው በዚህ መሠረት ማመልከቻ ሲያቀርብ ባለሥልጣኑ ይህ ሰው ሥራውን ያቆመ መሆኑንና በሁሉም
የታክስ ሕጎች የመመዝገብ ግዴታ የሌለበት መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ ለዚህ ሰው የጽሑፍ ማስታወቂያ
በመስጠት ምዝገባውን ይሰርዘዋል፡፡
• ምዝገባ የተሠረዘ መሆኑን የሚገልፀው ማስታወቂያ ማመልከቻው ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት
ለአመልካቹ መሰጠት የሚኖርበት ሲሆን፣ ባለሥልጣኑም የምዝገባ ይሰረዝልኝ ማመልከቻው ከቀረበበት ጊዜ
ጀምሮ ባሉት 90 ቀናት ውስጥ የታክስ ከፋዩን የታክስ ጉዳዮች በተመለከተ የመጨረሻ ኦዲት ሊያደርግ
ይችላል፡
• አንድ ሰው ምዝገባ እንዲሰረዝለት ጥያቄ ያላቀረበ እንደሆነ ባለሥልጣኑ ይህ ሰው ሥራውን ሙሉ በሙሉ
ማቆሙን እና ለታክስ ሕጐች ዓላማ የመመዝገብ ግዴታ የሌለበት መሆኑን እንዲሁም የተፈጥሮ ሰው ከሆነ
መሞቱን፣ ኩባንያ ከሆነም መፍረሱን፣ ወይም ሌላ ማንኛውም ሰው ሕልውናው የተቋረጠ መሆኑን
ሲያምንበት ለታክስ ከፋዩ ወይም ለታክስ እንደራሴው የጽሑፍ ማስታወቂያ በመስጠት ምዝገባውን ይሰርዛል፡
• ሆኖም የአንድ ሰው የምዝገባ መሰረዝ በሌላ ታክስ ሕግ አንድን የተለየ ታክስ የሚመለከት ሲሆን፣ በዚያ
የታክስ ሕግ ምዝገባ መሰረዝን በሚመለከት የሠፈሩትን ግዴታዎች ማሟላት ግዴታ ይሆናል፡፡
• ከግብር ከፋይነት እንዲሰረዝ ያልጠየቀ በየወሩ 1,000 ብር መቀጫ ይከፍላል (አንቀጽ 101 ን.አ 4)
18
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
• ስለታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008አንቀጽ 12 - 15)
ታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር
• ታክስ ከፋዮችን ለመለየት እንዲቻል ባለሥልጣኑ ለታክስ ሕጐች ዓላማ ሲባል ለተመዘገበ ሰው የታክስ ከፋይ
መለያ ቁጥር በሚል የሚታወቅ ቁጥር ይሰጣል፤ ታክስ ከፋዩም የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን የታክስ ሕጎች
በሚያዙት መሠረት መጠቀም አለበት፡፡
የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ስለመሰጠት
• ለሁሉም የታክስ ሕጐች አንድ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የሚሰጥ ሲሆን አንድ ታክስ ከፋይ በማንኛውም
ጊዜ አንድ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ብቻ ይኖረዋል፡፡
• ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የታክስ መለያ ቁጥር የሚሰጠው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ማስታወቂያ
በመስጠት ይሆናል፡
የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር አጠቃቀም
• የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የተሰጠው ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን በማንኛውም የታክስ ማስታወቂያ፣
ማስታወቂያ ወይም ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል በሚቀርብ ወይም ጥቅም ላይ በሚውል ሰነድ ወይም በታክስ
ሕግ መሠረት በሚዘጋጅ ሰነድ ላይ መግለጽ ይኖርበታል፤
• የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ለተሰጠው ሰው ብቻ የሚያገለግል ስለሆነ በሌላ ሰው ጥቅም ላይ ሊውል
አይገባም፤
• የዚህ አዋጅ አንቀጽ 103 ከታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ጋር የተገናኘ ቅጣቶችን አስቀምጧል፡፡
19
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ለውጦችን ስለማሳወቅ
• ማንኛውም የተመዘገበ ሰው
ስሙ፣ ቋሚ አድራሻው ወይም የፖስታ አድራሻው፣ የተቋቋመበት መተዳደሪያ ደንብ ወይም
ዋንኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም እንቅስቃሴዎቹ ከተለወጡ
ከባለሥልጣኑ ጋር ግንኙነት የሚያደርግበት የባንክ አድራሻ፣ የኤሌክትሮኒክ አድራሻ ከተለወጠ
ባለሥልጣኑ በመመሪያ የሚወሰናቸው ሌሎች ዝርዝሮች በተመለከተ ፣ ለውጥ ሲከሰት ለውጡ
በተከሰተ በ30 ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፤
የተመዘገበ ሰው የለውጥ ማስታወቂያ ሲያቀርብ ይህ ሰው በሌላ የታክስ ሕግ ለአንድ ለተለየ
ታክስ ካደረገው ምዝገባ ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ለውጦችን ማስታወቅን በተመለከተ
የተጣለበትን የማስታወቅ ግዴታ እንደተወጣ ይቆጠራል፡፡
ይህን ያልተወጣ
• በንግድ ሥራው ላይ ማንኛውንም ለውጥ ያላሳወቀ ብር 2ዐ,ዐዐዐ፣ የዚህ አዋጅ አንቀጽ 114 ን.አ 1
• የመመስረቻ ጽሁፍ (የመተዳደሪያ ደንብ) ወይም የነዚህን ማሻሻያዎች ያላቀረበ ላላቀረበበት ለእያንዳንዱ ወር
ወይም ለወሩ ከፊል ብር 1ዐ,ዐዐዐ ቅጣት ይከፍላል ፣ አንቀጽ 114 ን.አ 2
20
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
የታክስ ማስታወቂያዎችን ስለማቅረብ (የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 21 – 24)
ይህንን አንቀጽ ተፈፃሚ የምናደርገው በገቢ ግብር አዋጁ አንቀጽ 83 ላይ በተቀመጠው ግብርን የማሣወቅ ጊዜ
መነሻ በማድረግ ነው፡፡ (በገቢ ግብር አዋጁ አንቀጽ 83 መሰረት ደረጃ “ሀ” የግብር ዓመቱ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት የአራት ወራት ጊዜ ውስጥ
፣የደረጃ “ለ” የግብር ዓመቱ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ፣ የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋይ ለእያንዳንዱ በጀት ዓመት ከሀምሌ 1 ቀን እስከ
ሐምሌ 30 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ እንዲሁም ወርሃዊ ታክሶች በቀጣዩ ወር የግብሩን/የታክስ ማስታወቂያውን ማ ይኖርበታል፡፡)
• በታክስ ሕግ የታክስ ማስታወቂያ የማቅረብ ግዴታ የተጣለበት ሰው ማስታወቂያውን በፀደቀው ቅጽ እና በዚህ
አዋጅ መሠረት በሚወጣ ደንብ በተመለከተው አኳሃን ማቅረብ አለበት፤
 በታክስ አስተዳደር ደንብ ቁጥር 407/2009 አንቀጽ 8 መሰረት በሌላ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር
በኤሌክትሮኒክ ዘዴ በማስተላለፍ ወይም ባለስልጣኑ የሚሰጠውን መመሪያ በመከተል ወይም በሌላ
ማናቸውም ሁኔታ በአካል በመቅረብ ወይም በፓስታ ለባለስልጣኑ በመላክ
• ቀደም ሲል የቀረበው የታክስ ማስታወቂያ በታክስ ከፋዩ የተዘጋጀ የራስ ታክስ ማስታወቂያ ካልሆነ በስተቀር
ማንኛውም ታክስ ከፋይ ባለሥልጣኑ በሚሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ፡-
1/ አስቀድሞ ለባለሥልጣኑ ያቀረበውን የታክስ ማስታወቂያ የሚያሟላ የታክስ ማስታወቂያ፣ ወይም
2/ ባለሥልጣኑ በሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ የተመለከቱ መረጃዎችን የያዘ የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ
አለበት፡፡
21
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
የታክስ ማስታወቂያዎችን ስለማቅረብ…
• ባለሥልጣኑ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም በቀረበ የታክስ ማስታወቂያ አይገደድም፡፡ ስለሆነም
ባለሥልጣኑ ባገኘው ማንኛውም አስተማማኝ እና ሊረጋገጥ የሚችል መረጃ ላይ በመመሥረት ታክስ ከፋዩ
መክፈል ያለበትን የታክስ መጠን ሊወስን ይችላል፡፡
• የኤሌክትሮኒክስ የታክስ ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ታክስ ከፋይ
በሚያቀርበው የታክስ ማስታወቂያ ላይ መፈረም የሚኖርበት ሲሆን የታክስ ማስታወቂያውም፣
ማስታወቂያው እና ተያያዥ ሰነዶችም የተሟሉና ትክክለኛ መሆናቸውን ታክስ ከፋዩ የሚያረጋግጥበትን
መግለጫ መያዝ አለበት፡፡
• የውክልና ሥልጣን በህግ አግባብ የተሰጠው ከሆነ የታክስ ከፋዩ የታክስ ወኪል ወይም የታክስ እንደራሴው
የታክስ ማስታወቂያውን ሊፈርም እና የማረጋገጫ መግለጫ ሊሰጥ ይችላል፡፡
• የታክስ ማስታወቂያው በታክስ ከፋዩ የታክስ ወኪል ወይም በታክስ እንደራሴው የተፈረመ ሲሆን ታክስ ከፋዩ
የማስታወቂያውን ይዘት እንደሚያውቅ እና ስለማስታወቂያው የተሟላ እና ትክክለኛ ስለመሆኑ ማረጋገጫ
እንደሰጠ ይቆጠራል፡፡
• የታክስ ማስታወቂያ በወቅቱ ሣይቀርብ ቢቀር የዚህ አዋጅ አንቀጽ 104 ላይ የታክስ ማስታወቂያ ዘግይቶ
ማቅረብ ስለሚያስከትለው ቅጣት ተደንግጓል፡፡
22
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
የታክስ ማስታወቂያዎች አስቀድሞ ስለማቅረብ
• ሥራውን ያቋረጠ ማንኛውም ታክስ ከፋይ ሥራውን ያቋረጠ መሆኑን ሥራውን ካቆመበት ቀን ጀምሮ በ30 (ሰላሳ) ቀናት
ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሑፍ ማሳወቅ አለበት፡፡
• ይህ የሚመለከተው ታክስ ከፋይ ሥራውን ባቆመ በ60 (ስልሳ) ቀናት ውስጥ ወይም ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ በሚሰጠው
የጽሑፍ ማስታወቂያ በሚወስነው ከዚያ ባነሰ ጊዜ ውሰጥ፡
ታክስ ከፋዩ ሥራውን ላቆመበት የታክስ ጊዜ ወይም የታክስ ማስታወቂያ ጊዜው ላልደረሰ ከዚያ በፊት ለነበረ የታክስ ጊዜ
የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ፣ እና
በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው መሠረት ሊከፈል የሚገባውን ታክስ መክፈል አለበት፡፡
• ማንኛውም ታክስ ከፋይ ከኢትዮጵያ ሊወጣ ከሆነና የታክስ ከፋዩ ከኢትዮጵያ መውጣት በጊዜያዊነት አለመሆኑ የሚገመት
ከሆነ ታክስ ከፋዩ ከኢትዮጵያ ከመውጣቱ በፊት፡
የወቅቱን የታክስ ማስታወቂያ እና ከኢትዮጵያ በሚወጣበት ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ የማቅረቢያ ጊዜው ላልደረሰው
ከዚያ በፊት ለነበረው የታክስ ጊዜ የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ፣ እና
በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው መሠረት መከፈል የሚገባውን ታክስ መክፈል ወይም ታክሱ የሚከፈልበትን ሁኔታ
ለባለሥልጣኑ አጥጋቢ በሆነ አኳሃን ማመቻቸት፣አለበት፡፡
• በማንኛውም የታክስ ጊዜ ታክስ ከፋዩ የታክስ ጊዜውን የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ በሚገባው ጊዜ አያቀርብም ብሎ ማመን
የሚያስችል ምክንያት ሲኖረው ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የጽሑፍ ማስታወቂያ በመስጠት፡-
ታክስ ከፋዩ ወይም የታክስ እንደራሴው የታክስ ጊዜው የታክስ ማስታወቂያ ማቅረቢያ ጊዜ ባይደርስም ባለሥልጣኑ
በሰጠው ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ እንዲያቀርብ፣ እና
በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው የተመለከተውን ታክስ ባለሥልጣኑ በሰጠው ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ
እንዲከፍል፣ ሊያዝ ይችላል፡፡
• ታክስ ከፋዩ ከአንድ የታክስ ዓይነት በላይ የሚመለከተው ከሆነ ይህ አንቀጽ ለእያንዳንዱ ታክስ በተናጠል ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
23
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ስለ ሠነዶች (የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ አንቀጽ 17-2ዐ)
• መዝገብ የመያዝ ግዴታዎች
ይህ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አንቀጽ የገቢ ግብር አዋጁ 979/2008 አንቀጽ 82 ላይ የተደነገገውን ለማስተዳደር የሚረዳ ነው፡፡
• ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል አንድ ታክስ ከፋይ በታክስ ሕግ መያዝ ያለባቸውን ሰነዶች በኤሌክትሮኒክ መልክ ጨምሮ የመያዝ
ግዴታ ያለበት ሲሆን እነዚህም ሰነዶች የሚያዙት፡
1/በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ፣ 2/በኢትዮጵያ ውስጥ፤ እና 3/የታክስ ከፋዩን የታክስ ግዴታ በግልጽ ለማረጋገጥ በሚቻልበት
ሁኔታ፣ መሆን አለበት፡፡
• በታክስ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር አንድ ታክስ ከፋይ ከላይ የተመለከቱትን ሰነዶች ከሚከተሉት ረጅም ለሆነው
ጊዜ ይዞ የማቆየት ግዴታ አለበት፡-
1/በንግድ ሕግ ለተወሰነው የሰነድ መያዣ ጊዜ ርዝማኔ /አዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀጽ 66 “ማንኛውንም የሒሣብ መዝገቦችና
የሒሣብ ሰነዶች የመጨረሻው ጽህፈት ከተፃፈባቸው ቀን ጀምሮ ወይም ሰነዶቹ ከተፃፋበት ቀን አንስቶ ወደፊት ላሉት 10 ዓመታት ድረስ ጠብቆ ማኖር ይገባል” ፣ ወይም
2/ሰነዶቹ አግባብነት በሚኖራቸው የታክስ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ ለባለሥልጣኑ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ለአምስት ዓመታት፣
ነገር ግን በአዋጁ መሠረት ለሚደረግ ክርክር ወይም ከላይ ከተመለከተው ጊዜ በፊት ተግባራዊ በሆነ ሕግ መሠረት
ለሚደረግ ክርክር ሰነዱ የሚያስፈልግ ሲሆን ታክስ ከፋዩ ሁሉም ክርክሮች እስከሚጠናቀቁ ጊዜ ድረስ ሰነዱን ይዞ
የማቆየት ግዴታ አለበት፡፡
• ሰነዱ በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ ካልቀረበ በባለሥልጣኑ በጹሁፍ በሚሰጥ ማስታወቂያ በሚወሰነው ጊዜ
ውስጥ ሰነዱ በባለሥልጣኑ ተቀባይነት ባለው ተርጓሚ በታክስ ከፋዩ ወጪ ወደ አማርኛ ወይም ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ
ተተርጉሞ እንዲቀርብ ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩን ሊያዘው ይችላል፡፡
• የሂሣብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 176/2014 በዝርዝር ይመልከቱ፡፡
• የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 102 ሰነዶችን ባለመያዝ የሚጣል ቅጣትን ደንግጓል፡፡
24
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ሪፖርት ማድረግ (Reporting)
በአግባቡ የቀረበ የታክስ ማስታወቂያ
• ተቃራኒ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም ቀርቧል የተባለ የታክስ ማስታወቂያ በታክስ ከፋዩ
ወይም በታክስ ከፋዩ ፈቃድ እንደቀረበ ይቆጠራል፡፡
ሰነዶችን ስለመመርመር
• በታክስ ሕግ መሰረት ሰነዶችን እንዲይዝ የሚገደድ ታክስ ከፋይ ሰነዱን ይዞ እንዲቆይ በሚጠበቅበት በማንኛውም
ምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ሰነዶቹን ለባለሥልጣኑ ምርመራ ዝግጁ የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡
የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች
• ባለሥልጣኑ፡- በማናቸውም ሁኔታ ታክስ ከፋዩ ዜሮ መጠንን ጨምሮ ለታክስ ጊዜው መክፈል የሚገባው የታክስ መጠን
በትክክል የተሰላ መሆኑን፣
ለማረጋገጥ በሚያገኘው ማስረጃ መሠረት ማንኛውንም የታክስ ስሌት (“የመጀመሪያው የታክስ ስሌት” ተብሎ
የሚጠቀስ) በመለወጥ ፣ በመቀነስ ወይም በመጨመር ሊያሻሽል ይችላል፡፡
• አግባብነት ባለው የታክስ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር፣ ባለሥልጣኑ ማንኛውንም የታክስ ስሌት፡-
1) በማንኛውም ጊዜ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም የማጭበርበር ድርጊት ሲፈጸም ወይም በከፍተኛ ሁኔታ ወይም
በማወቅ የተፈፀመ የቸልተኝነት ድርጊት ሲኖር፣ ወይም
2) በሌላ በማናቸውም ሁኔታ፡-
ታክስ ከፋዩ በራሱ የሚያሰላው የታክስ ስሌት ሲሆን ታክስ ከፋዩ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ
በሚቆጠር 5(አምስት) ዓመት ውስጥ፣
ለሌላ ማንኛውም የታክስ ስሌት ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ከሰጠበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር
5(አምስት) ዓመት ውስጥ፣ ሊያሻሽል ይችላል፡፡
25
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ታክስ ከፋዩ ራሱ ያዘጋጀው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል ስለሚቀርብ ማመልከቻ
• የራሱን የታክስ ስሌት ያዘጋጀ ታክስ ከፋይ ያቀረበውን በራስ የተዘጋጀ የታክስ ማስታወቂያ ባለሥልጣኑ እንዲያሻሸልለት
ለባለሥልጣኑ ሊያመለክት ይችላል፡፡ በዚህ መሠረት የሚቀርበው ማመልከቻ፣
ታክስ ከፋዩ ራሱ አዘጋጅቶ ባቀረበው የታክስ ማስታወቂያ ላይ ሊደረጉ ይገባል ብሎ የሚያምንባቸውን ማሻሻያዎችን እና
ማሻሻያዎቹን ማድረግ አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያቶች መግለጽ፣ እና
• ታክስ ከፋዩ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 5 /አምስት ዓመት/ ውስጥ መቅረብ፣
ይኖርበታል፡፡
• በዚህ ድንጋጌ መሠረት ማመልከቻ ሲቀርብለት ማመልከቻው በቀረበለት በ120 (አንድ መቶ ሃያ) ቀናት ውስጥ ባለሥልጣኑ
በሚያወጣው መመሪያ መሠረት በታክስ ከፋዩ ተዘጋጅቶ የቀረበው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል መወሰን ወይም ማመልከቻውን
ውድቅ ማድርግ አለበት፡፡
• ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ ራሱ ያቀረበው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል የወሰነ እንደሆነ፣
የታክስ ስሌት ማሻሻያው ባለስልጣኑ የታክስ ከፋዩ ኪሣራ በትክክል የተሰላ መሆኑን፣ ታክስ ከፋዩ በታክስ ጊዜው
የከፈለው የግብዓት ተጨማሪ እሴት ታክስ በትክክል የተሰላ መሆኑን እና በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ታክስ ከፋዩ ዜሮ
መጠንን ጨምሮ ለታክስ ጊዜው መክፈል የሚገባውን የታክስ መጠን በትክክል የተሰላ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚያገኘው
ማስረጃ መሰረት ማንኛውንም የመጀመሪያ የታክስ ስሌት ተብሎ የሚጠቀሰውን በመለወጥ፣ በመቀነስ፣ ወይም
በመጨመር ሊያሻሽል ይችላል፡
• ይህ ታክስ ከፋዩ የሚያቀርበውን የራስ ታክስ ስሌት እንዲሻሻል ስለሚፈቀድበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር
144/2011 የሚፈጸም ይሆናል፡፡ በዚህ መመሪያ በ3ምክንያቶች ማሻሻያው ይከለከላል፡ ነገር ግን እነዚህ ቢኖሩም ባለስልጣኑ
በራሱ አነሣሽነት የተሻሻለ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ሊሰጥ ይችላል፡፡
26
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ከታክስ ጋር በተገናኘ የሚፈጠር አለመግባባት /Disputes/ - እንዴት እንፈታቸዋለን? የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 52-60/
በዚህ አዋጅ ከታክስ ጋር በተገናኘ የሚፈጠር አለመግባባት በሚፈታበት አግባብ በተቀመጠ ክፍል /የአዋጁ ክፍል ዘጠኝ/ በተደነገገው ሥነ-ሥርዓት
መሰረት ካልሆነ በስተቀር
የታክስ(የተሻሻለ)ወይም ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል ውሳኔ ወሳኝ እና የመጨረሻ በመሆኑ በማናቸውም ሁኔታ በኮሚሽኑ ወይም በፍርድ ቤት
ወይም በሌላ የዳኝነት ሥነ ሥርዓት ተቃውሞ ሊቀርብበት አይችልም፡፡
ውሳኔ ላይ ስለሚቀርብ የቅሬታ ማስታወቂያ
 የውሳኔው ማስታወቂያ በደረሰው በ21 ቀናት ውስጥ የቅሬታ ማስታወቂያ በጽሑፍ ማቅረብ ይችላል፡፡
 ቅሬታ የቀረበበት የታክስ ውሳኔ በተሻሻለ የታክስ ስሌት ላይ ከሆነ የታክስ ከፋዩ የተሻሻለውን የታክስ ስሌት የመቃወም መብት የመጀመሪያውን
የታክስ ስሌት በመለወጥ፣በመቀነስ ወይም በመጨመር በተደረገው ማሻሻያ ላይ ብቻ የተገደበ ይሆናል፡፡
 በታክስ ከፋይ የቀረበ የቅሬታ ማስታወቂያ በአግባቡ እንደቀረበ የሚቆጠረው ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ብቻ ነው፡-
ሀ) የቅሬታ ማስታወቂያው ታክስ ከፋዩ የታክስ ውሳኔውን የሚቃወምበትን ምክንያቶች፣ ታክስ ከፋዩ ውሳኔውን ለማስተካከል
ሊደረጉ ይገባል ብሎ የሚያምንባቸውን ማሻሻያዎች እና እነዚህን ማሻሻያዎች ማድረግ አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያቶች በትክክል የሚገልጽ
ከሆነ፣
ለ) ቅሬታው ከታክስ ስሌት ጋር የተገናኘ ከሆነ ታክስ ከፋዩ በታክስ ስሌቱ መሠረት መከፈል ያለበትን እና በቅሬታ
ማስታወቂያው ተቃውሞ ያላቀረበበትን ታክስ የከፈለ እንደሆነ ነው፡፡
ሐ) በታክስ ውሳኔው ላይ ቅሬታ ቢኖረውም ታክሱን ከፍሎ የቅሬታ ማስታወቂያ ማቅረብን የመረጠ ከሆነ የተወሰነበትን ታክስ
ከከፈለ ነው፡፡
• የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ከማለፉ በፊት ታክስ ከፋዩ በታክስ ውሳኔ ላይ የቅሬታ ማስታወቂያ የሚያቀርብበት ጊዜ እንዲራዘምለት ለባለሥልጣኑ
የጽሑፍ ማመልከቻ ማቅረብ ይችላል፡፡ ባለሥልጣኑ፡-
ሀ) ታክስ ከፋዩ በኢትዮጵያ ውስጥ ያልነበረ በመሆኑ፣ በህመም ምክንያት ወይም በሌላ አጥጋቢ ምክንያት በተወሰነው ጊዜ ውስጥ የቅሬታ
ማስታወቂያውን ማቅረብ አለመቻሉ፣ እና
ለ) የቅሬታ ማስታወቂያውን ለማቅረብ በታክስ ከፋዩ በኩል ምክንያታዊ ያልሆነ መዘግየት አለመኖሩን፣ ሲያምንበት የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜው
ካበቃበት ቀን ጀምሮ ከአሥር ቀናት ላልበለጠ ጊዜ ሊያራዝም ይችላል፡፡
27
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ውሳኔ ላይ ስለሚቀርብ የቅሬታ ማስታወቂያ…
• ባለሥልጣኑ በሥራ ክፍሉ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበውን ቅሬታ በሙሉ ወይም በከፊል በመቀበል ወይም ውድቅ
በማድረግ ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን ውሳኔውም በቅሬታ ላይ የተሰጠ ውሳኔ” ተብሎ ይጠቀሳል፡፡
• ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ ቅሬታ ካቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 180 ቀናት ውስጥ በቅሬታው ላይ ውሳኔ ካልሰጠ ታክስ ከፋዩ ይግባኙን ለታክስ
ይግባኝ ኮሚሽን ማቅረብ ይችላል እንዲሁም ይግባኝ ሊቀርብበት በሚችል ውሳኔ ላይ ቅር የተሰኘ ታክስ ከፋይ የይግባኝ ማስታወቂያውን ለታክስ
ይግባኝ ኮሚሽን ሊያቀርብ ይችላል፡፡
 በታክስ ስሌት ላይ ከቀረበ ቅሬታ ጋር በተገናኘ በታክስ ከፋይ ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የሚቀርብ የይግባኝ ማስታወቂያ በአግባቡ ቀርቧል ሊባል
የሚችለው፡-በክርክር ላይ ያለ ታክስ 50% የተከፈለ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
 በክርክር ላይ ያለ ታክስ ከታክሱ ጋር በተገናኘ ሊከፈል የሚገባውን ቅጣትና የዘገየ ክፍያ ወለድን አይጨምርም፡፡
• ኮሚሽኑ በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ግብር ከፋይ የኮሚሽኑ የውሳኔ ማስታወቂያ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ የይግባኝ ማስታወቂያውን
ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡
• የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ እንዲራዘምለት በጽሑፍ ማመልከቻ ለሚጠይቅ ግብር ከፋይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጊዜውን ሊያራዝመው
ይችላል፡፡
• በታክስ ስሌት ላይ ከቀረበ ቅሬታ ጋር በተገናኘ በታክስ ከፋይ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርብ የይግባኝ ማስታወቂያ በአግባቡ ቀርቧል
ሊባል የሚችለው በክርክር ላይ ያለ ታክስ 75% የተከፈለ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
• ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚቀርበው በሕግ ጉዳዮች ላይ ብቻ ሲሆን የይግባኝ ማስታወቂያውም በቀረበው ይግባኝ የሚነሱትን የሕግ
ጉዳዮች መግለጽ አለበት፡፡
• የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ግብር ከፋይ የፍርድ ቤቱ የውሳኔ ማስታወቂያ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ የይግባኝ
ማስታወቂያውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡
28
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ታክስ/ግብር መክፈል (Payment)
ታክስን ስለመሰብሰብና ማስከፈል / የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 30-48/
ታክስ ለመንግሥት የሚከፈል ስለመሆኑ
• በታክስ ሕግ መሠረት በታክስ ከፋዩ ሊከፈል የሚገባውና የመክፈያ ጊዜው የደረሰ ታክስ ለመንግሥት የሚከፈል ዕዳ ስለሆነ ለባለሥልጣኑ መከፈል
አለበት፡፡
• በኤሌክትሮኒክስ አከፋፈል ዘዴ ታክስ እንዲከፍል በባለሥልጣኑ የተጠየቀ ታክስ ከፋይ ባለሥልጣኑ ሌላ የአከፋፈል ዘዴ
እንዲጠቀም በጽሑፍ ካልፈቀደለት በስተቀር ክፍያውን የሚፈጽመው በኤሌክትሮኒክስ አከፋፈል ዘዴ ይሆናል፡፡
ይህን ባይጠቀምስ? በአዋጁ አንቀጽ 111 መሰረት የኤሌክትሮኒክስ የታክስ ሥርዓትን አለመከተል የሚያስከትለው ቅጣት ይጣልበታል፡፡
• ታክስ ከፋዩ ታክሱን መክፈል ባለበት ጊዜ ካልከፈለ በህጉ ወለድ ይጠየቃል፤ እንዲሁም በአዋጁ አንቀጽ 105 መሰረት የተቀመጠውን ታክስ ዘግይቶ
መክፈል የሚያስከትለውን ቅጣት ይቀጣል ፤በተጨማሪም ባለሥልጣኑ ያልተከፈለውን ታክስ ለማስከፈል በሚወስደው እርምጃ ምክንያት
ለሚያወጣው ማንኛውም ወጪ ኃላፊ ይሆናል፡፡
• የመክፈያ ጊዜው የደረሰ ታክስ የመክፈያ ጊዜው እንዲራዘም ለባለሥልጣኑ የጽሑፍ ማመልከቻ ሊቀርብ ይችላል፡-
 ማመልከቻ በሚቀርብበት ጊዜ ባለሥልጣኑ በቂ ምክንያት መኖሩን ካረጋገጠ
ሀ) ለታክስ ከፋዩ የታክስ መክፈያ ጊዜውን ሊያራዝምለት፣ ወይም
ለ) ባለሥልጣኑ በሚወሰነው መሠረት ታክሱን በመከፋፈል በተወሰነ ጊዜ ውስጥእንዲከፍል ሊያደርገው፣ ይችላል፡፡
 ለቀረበው ማመልከቻ የሰጠውን ውሳኔ የሚገለጽ የጽሑፍ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጠዋል፡፡
 ታክሱን በመከፋፈል በተወሰነ ጊዜ ውስጥ እንዲከፍል የተፈቀደለት ታክስ ከፋይ የአንድን ጊዜ ክፍያ ካልከፈለ ታክስ ከፋዩ ክፍያውን ባቆመበት
ጊዜ ያለውን ቀሪ ክፍያ በሙሉ እንዲከፍል ባለሥልጣኑ ወዲያውኑ እርምጃ ሊወስድ ይችላል፡፡
 በዘገየው ክፍያ ላይ ከመጀመሪያ የታክስ መክፈያ ቀን ጀምሮ የሚታሰብ ወለድ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
ዝርዝር አፈፃፀሙ በክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ መመሪያ ቁጥር 142/2011 ተመላክቷል
29
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
የአከፋፈል ቅደም ተከተል
• ታክስ ከፋዩ የፈፀመው ክፍያ መክፈል ከሚገባው ጠቅላላ የታክስ፣ የቅጣትና የወለድ መጠን ያነሰ በሚሆንበት ጊዜ
የተከፈለው ገንዘብ የሚሸፍነው ዕዳ ቅደም ተከተልን በተመለከተ፡-
ሀ) በመጀመሪያ ዋናውን የታክስ ዕዳ ለመክፈል፤
ለ) ቀጥሎ ክፍያ ለዘገየበት የሚከፈል ወለድ፣
ሐ) ቀሪው ገንዘብ ለቅጣት መክፈያ ይውላል፡፡
• ከአንድ በላይ የታክስ ዕዳ የሚፈለግበት ግብር ከፋይ ክፍያው የሚሸፍነው ዕዳ ቅደም ተከተል ዕዳው በተፈጠረበት ጊዜ ቅደም
ተከተል መሠረት ይሆናል ፡፡
ለታክስ አከፋፈል የሚቀርብ ዋስትና
• ባለሥልጣኑ የመንግሥትን ገቢ ለመጠበቅ አስፈላጊ መስሎ ሲታየው አስፈላጊ ነው በሚለው መጠንና አኳኋን ታክስ ከፋዩ
ዋስትና እንዲያቀርብ ሊያስገድደው ይችላል፡፡ ታክስ ከፋዩ ዋስትና እንዲያቀርብ የሚጠየቀውም፡-
ሀ) የመክፈያ ጊዜው ለደረሰ ወይም የመክፈያ ጊዜው ለሚደርስ ታክስ መክፈያ፣ ወይም
ለ) በታክስ ሕግ መሠረት ተመላሽ ለሚጠይቅ ታክስ ከፋይ ቅድመ ሁኔታ ይሆናል፡፡
• በዚህ መሠረት የሚሰጥ ዋስትና ባለሥልጣኑ የሚጠይቃቸው ተገቢ ቅድመ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በጥሬ ገንዘብ
ወይም በባንክ ዋስትና ሊሰጥ ይችላል፡፡
• ታክስ ከፋዩ ዋስትና የማቅረብ ግዴታ የሚኖርበት ባለሥልጣኑ፡-
ሀ) የሚፈለገው የዋስትና መጠን፣
ለ) ዋስትናው የሚቀርብበትን አኳኋን፣ እና
ሐ) ዋስትናው የሚቀርብበትን ቀን የሚገልጽ የጽሑፍ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ የሰጠ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
• ያላቀረበው የዋስትና መጠን የታክስ ከፋዩ ያልተከፈለ ታክስ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህም በታክስ ክሊራንስ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 147/2011
እና በተእታ ተመላሽ አሰጣጥ መመሪያ 148ና ሌሎች የተመላሽ አፈፃፀም መመሪያዎች መሰረት የተመላከቱ መብቶችን ያዘገያል/ያሣጣል፤
30
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ለዘገየ ክፍያ የሚከፈል ወለድ/አ.37/
• በታክስ መክፈያ ጊዜው ወይም ከዚያ በፊት ታክሱን ያልከፈለ ታክስ ከፋይ ታክሱ መከፈል ከነበረበት ቀን ጀምሮ ተከፍሎ
እስካለቀበት ቀን ድረስ ባልተከፈለው መጠን ላይ ለዘገየው ክፍያ ወለድ የመክፈልግዴታ አለበት፡፡
• የዘገየ ክፍያ የወለድ መጣኔ በንግድ ባንኮች ሥራ ላይ በዋለው ከፍተኛው የማበደሪያ ወለድ መጣኔ ላይ 15% (አሥራ
አምስት በመቶ) ተጨምሮበት ይሆናል፡፡
• በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 105 መሠረት ታክስን በመክፈያ ጊዜው ባለመክፈል ከሚጣለው
ቅጣት በተጨማሪ ይሆናል፡፡
• በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ በነጠላ ወለድ የሚሰላ ሲሆን የሚታሰበውም በየቀኑ ይሆናል፡፡
• ታክስ ከፋዩ የታክስ ዕዳ የታክስ ስሌት ማስታወቂያን እስከተሰጠበት ቀን ድረስ መክፈል የሚጠበቅበትን የዘገየ ክፍያ ወለድን
ጨምሮ በማስታወቂያው የተመለከተውን የታክስ ዕዳ በሙሉ በማስታወቂያው በተገለጸው የመክፈያ ቀን የከፈለ ከሆነ
ማስታወቂያው በተሰጠበት እና ክፍያው በተፈፀመበት መካከል ላለው ጊዜ የዘገየ ክፍያ ወለድ አይታሰብም፡፡
• ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ በሚከፈል ታክስ ወይም በሁለተኛ ደረጃ ኃላፊነት በሚከፈል ታክስ ላይ የሚታሰብ የዘገየ ክፍያ
ወለድ መከፈል ያለበት ይኸው ኃላፊነት ባለበት ሰው ብቻ በመሆኑ ከሌላ ማንኛውም ሰው ሊጠየቅ አይችልም፡፡
• በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ ጠቅላላ መጠን ከታክስ ከፋዩ የታክስ ዕዳ ሊበልጥ አይችልም፡፡
31
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል
• ማንኛውም ታክስ ከፋይ ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ እንደሆነ ባለሥልጣኑ ያልተከፈለውን ታክስ እና ታክሱን ለማስከፈል የሚወሰደው
እርምጃ የሚያስከትለውን ወጪ ማስከፈል እንዲቻል በታክስ ከፋዩ ሀብት ላይ የባለሥልጣኑን የዋስትና መብት እንዲመዘግብ ንብረቱን
ለመዘገበው አካል እንደሚያመለክት የሚገልጽ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጣል፡፡
• ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ ማስታወቂያው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ታክሱን ያልከፈለ እንደሆነ፣ ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ በሰጠው
ማስታወቂያ የተመለከተው የታክስ ከፋዩ ሀብት ላልተከፈለው ታክስ እና ታክሱን ለማስከፈል ለሚደረግ ወጪ በዋስትና እንዲያዝ ንብረቱን
ለመዘገበው አካል የጽሁፍ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡
• ባለሥልጣኑ ታክስ የሚፈለግበት ሰው ሀብት በዋስትና ተይዞ እንዲቆይ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ መዝጋቢው ባለሥልጣን ሀብቱ በዋስትና እንዲያዝ
የደረሰውን የጽሑፍ ትዕዛዝ ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይጠይቅ እንደማንኛውም በሀብቱ ላይ እንዳለ የንብረት መያዣ ወይም የዋስትና ሰነድ
ይመዘግባል፤
የተረካቢዎች ግዴታዎች
• ማንኛውም ተረካቢ የአንድን ታክስ ከፋይ ሀብት በኢትዮጵያ ውስጥ ተረካቢ ሆኖ ከተሾመ ወይም ሀብቱ በይዞታው ሥር ከገባ ከሁለቱ
ከሚቀድመው ጊዜ ጀምሮ ባሉት አሥራ አራት ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሑፍ ማሳወቅ አለበት፡፡
• ባለሥልጣኑ ሀብቱ በተረካቢው ቁጥጥር ሥር ባለው ታክስ ከፋይ ያልተከፈለውን የታክስ ዕዳ እና ወደፊት የሚከፈለውን የታክስ መጠን በመወሰን
የጽሑፍ ማስታወቂያ በደረሰው በ 30 ቀናት ውስጥ ለተረካቢው ማሳወቅ አለበት፡፡
• ተረካቢው
ሀ) ከባለሥልጣኑ አስቀድሞ ፈቃድ ካላገኘ በስተቀር በእጁ የሚገኘውን የታክስ ከፋዩን ሀብት ማስታወቂያ ከባለስልጣኑ ተሰጥቶት የ30
ቀናት ጊዜ ከማለፍ በፊት መሸጥ ወይም በማናቸውም ሁኔታ ማስተላለፍ አይችልም፡፡
ለ) ከሀብቱ ሽያጭ ገንዘብ ላይ ባለሥልጣኑ የገለጸውን የታክስ መጠን ወይም ባለሥልጣኑ የተስማማበትን የታክስ መጠን ቀንሶ ማስቀመጥ
አለበት፡፡ እንዲሁም
ሐ) የሀብቱ ባለቤት በሆነው ታክስ ከፋይ መከፈል ላለበት ታክስ ከሀብቱ ሽያጭ ገቢ ተቀንሶ መቀመጥ ባለበት የገንዘብ መጠን ልክ በግል
ተጠያቂ ይሆናል፡፡
• ሆኖም ተረካቢው እንዲከፍል ከተጠየቀው ታክስ በማስቀደም የሚከተሉትን ክፍያዎች ከመፈፀም አይከለክለውም፡-
ሀ) በሕግ የቅድሚያ መብት ያለውን ዕዳ፣
ለ) የተረካቢውን አበል ጨምሮ ተረካቢው በተረካቢነት ችሎታው የሚያወጣቸውን ወጪዎች፣
32
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል…
ሀብትን ስለመያዝ /41/
• ባለሥልጣኑ ታክሱን በመክፈያ ጊዜው ላልከፈለ ታክስ ከፋይ የሚፈለግበትን ታክስ ማስጠንቀቂያ በደረሰው በ30 ቀናት
ውስጥ ካልከፈለ የታክስ ከፋዩ ሀብት እንዲያዝ ትዕዛዝ የሚሰጥ መሆኑን የሚገልጽ ማስጠንቀቂያ ለታክስ ከፋዩ ሊሰጠው
ይችላል፡፡
• ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ የሚፈለግበትን ታክስ የሚከፍል ለመሆኑ ስጋት መኖሩን ካረጋገጠ የመያዣ ትዕዛዙን ወዲያውኑ
ሊሰጥ ይችላል፡፡
• በተሰጠው ማስጠንቀቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ታክሱን ካልከፈለ ወይም ስጋት መኖሩ ሲረጋገጥ ባለሥልጣኑ የመያዣ
ትዕዛዙን ለታክስ ከፋዩ ሊሰጥ ወይም የታክስ ከፋዩን ሀብት በይዞታው ሥር ባደረገ በማንኛውም ሰው ላይ ሊያስተላልፍ
ይችላል፡፡
• የመያዣ ትዕዛዙ ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት በስተቀር በማንኛውም የታክስ ከፋዩ ሀብት ላይ ተፈጻሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ሀ)
በሀብቱ ላይ የቀደምትነት መብት ባላቸው የገንዘብ ጠያቂዎች በተያዘ ንብረት፣
ለ) በማናቸውም የፍርድ ሂደት ዕገዳ በተደረገበት ወይም የአፈፃፀም ትአዛዝ በተሰጠበት ንብረት፣
ሐ) በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ሊታገድ በማይችል ንብረት፣
• በታክስ ከፋዩ ንብረት ላይ የመያዣ ትዕዛዝ ከተሰጠ ወይም የሚሰጥ ከሆነ ባለሥልጣኑ በጽሑፍ በሚሰጥ ማስታወቂያ
የሚያዘውን ሀብት በሚመለከት በማስረጃነት ሊያገለግል የሚችል ማንኛውንም ሰነድ ወይም መግለጫ የያዘ ማንኛውም
ሰው ይህን ሰነድ ወይም መግለጫ ለባለሥልጣኑ እንዲያቀርብ ሊጠይቀው ይችላል፡፡
• ባለሥልጣኑ የታክስ ከፋዩን ንብረት በሚይዝበት ጊዜ የሚከተሉትን ነጥቦች የያዘ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጠዋል፡-
ሀ) የተያዘውን ንብረት እና ያልተከፈለውን የታክስ መጠን፣
ለ) ታክስ ከፋዩ በማስታወቂያው በተገለጸው ሀብቱ ተይዞ በሚቆይበት ጊዜ ውስጥ የሚፈለግበትን ታክስ የማይከፍል
ከሆነ ሀብቱን እንደሚሸጠው፤
33
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል…
• በፋይናንስ ተቋማት የተቀመጠ ገንዘብ እና ንብረት ይዞ ለማቆየት ይቻላል/42/
• ያልተከፈለን ታክስ ከሦስተኛ ወገኖች ለማስከፈል ይቻላል/43/
• ከሀገር መውጣትን ለመከልከል የሚሰጥ ትዕዛዝ ሊተላለፍ ይችላል (ታክስ ከፋዩ ወይም የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ
ወይም በአንድ ኩባንያ ወሳኝ ድምጽ ያለው አባል) /44/
• የንግድ ድርጅትን ለጊዜው ለማሸግ ይችላል /45/ አንድ ታክስ ከፋይ በተደጋጋሚ፡-
ሀ) በግብር ሕግ መሠረት የሚፈለግበትን ሰነድ ሳይዝ ሲቀር፣ወይም
ለ) ታክሱን በመክፍያ ጊዜው ሳይከፍል ሲቀር ይሆናል፡፡
• አንድ ታክስ ከፋይ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራ ጋር በተገናኘ ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ ያለበት እንደሆነ እና የንግዱን ሀብቶች
በሙሉ ወይም በከፊል ግንኙነት ላለው ሰው ያስተላለፈ እንደሆነ ከንግዱ ሀብት ጋር ተያይዞ ያልተከፈለውን ዕዳ ሀብቱ
የተላለፈለት ሰው የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል፡፡ ይህ ግን ባለሥልጣኑ የተላለፈውን የታክስ ዕዳ በሙሉ ወይም በከፊል
ከሀብት አስተላላፊው ላይ እንዳይጠይቅ አያግደውም፡፡
• አንድ ድርጅት ታክሱን በመክፈያው ጊዜ ውስጥ ያልከፈለ እንደሆነ ታክሱ ባልተከፈለበት ጊዜ ወይም ታክሱ ከመከፈሉ በፊት
ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ሥራ አስኪያጅ የነበረ ማንኛውም ሰው ላልተከፈለው ታክስ ከድርጅቱ ጋር የአንድነትና
የነጠላ ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡
 ከላይ የተጠቀሰው በሚከተሉት ሁኔታዎች ተፈፃሚ አይሆንም፡-
ሀ) ድርጅቱ የሚፈለግበትን ግብር ሳይከፍል የቀረው ከሥራ አስኪያጁ ፈቃድ ወይም ዕውቀት ውጭ የሆነ
እንደሆነ፣ እና
ለ) ሥራ አስኪያጁ ድርጅቱ ግብር ላለመክፈል የሚያደርገውን ጥረት ለመከላከል ተገቢውን ትጋት አሳይቶ
የሆነ እንደሆነ ነው፡፡
34
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ለታክስ ክፍያዎች የሚሰጥ ማካካሻ /49-50/
• ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ ለቀረ ታክስ እና በቅድሚያ ለተከፈለ ታክስ ሊገኝ የሚገባ ማካካሻ በታክስ ዓመቱ ከሚፈለግ
የገቢ ግብር ዕዳ በሚበልጥበት ጊዜ፤ በብልጫ የታየውን ገንዘብ በሚከተለው ቅደም ተከተል ሥራ ላይ ይውላል፡፡
ሀ) በመጀመሪያ በገቢ ግብር አዋጅ መሠረት ለሚፈለግ ማንኛውንም ታክስ ፤
ለ) ቀሪው ታክስ ከፋዩ በሌላ በማንኛውም የታክስ ሕግ የሚፈለግበትን ታክስ ለመክፈል ይውላል፡፡
ሐ) ከዚህ ሁሉ ተራፊ ገንዘብ ካለም ታክስ ከፋዩ በጽሑፍ የተመላሽ ጥያቄ ካቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 90
ቀናት ውስጥ ለታክስ ከፋዩ ይመለስለታል፡፡
• ታክስ ከፋዩ በጽሑፍ ስምምነቱን ከገለጸ ወደፊት ለሚመጣ ማንኛውም የታክስ እዳ መክፈያነት ሊሸጋገር ይችላል፡፡
• ባለሥልጣኑ ተራፊውን ገንዘብ ለታክስ ከፋዩ ካልከፈለ፤ 90ናኛው ቀን ካለቀ ጀምሮ ተራፊው ገንዘብ እስከሚመለስበት ቀን
ባለው ጊዜ ውስጥ ታክስ ከፋዩ ወለድ የማግኘት መብት አለው፡፡
• ነገር ግን ባለሥልጣኑ ታክስ በስህተት ተመላሽ ያደረገ እንደሆነ ታክስ ከፋዩ በባለሥልጣኑ ሲጠየቅ በመጠየቂያ ሰነድ
በተጠቀሰው ቀን በስህተት የተመለሰለትን ገንዘብ ለባለሥልጣኑ መልሶ መክፈል አለበት፡፡
• ተመላሽ በሚጠይቀው ታክስ ከፋይ አሳሳችነት ገንዘብ በስህተት የተመለሰ እንደሆነ ታክስ ከፋዩ ገንዘቡ በስህተት
በተመለሰበትና በስህተት የተመለሰው ገንዘብ ተመልሶ ለባለሥልጣኑ በተከፈለበት ቀን መካከል ላለው ጊዜ ወለድ የመክፈል
ኃላፊነት አለበት፡፡
35
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ከባድ ችግር ሲያጋጥም ስለሚሰጥ የታክስ ምህረት /51/
• ይህ ተፈጻሚ የሚሆነው ሚኒስትሩ፡-
ሀ) ባልተጠበቀ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ጥፋት ምክንያት ወይም ከታክስ ከፋዩ ቸልተኝነት ወይም ማንኛውም ጥፋት
ጋር ባልተገናኘ ሁኔታ የተፈጠረ ከባድ የግል ችግር ምክንያት ታክስ ከፋዩ የሚፈለግበትን ታክስ በሙሉ እንዲከፍል ማድረግ
የማይቋቋመው ከባድ ችግር የሚያስከትልበት መሆኑን፣ ወይም
ለ) በታክስ ከፋዩ ሞት ምክንያት ታክስ ከፋዩ መክፈል የሚኖርበትን ታክስ በሙሉ እንዲከፈል ማድረግ በታክስ ከፋዩ
ጥገኞች ላይ ከባድ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ሲያምንበት ነው፡፡
• በዚህ ጊዜ ሚኒስትሩ ታክስ ከፋዩ መክፈል የሚኖርበትን ታክስና ከዚህ ታክስ ጋር በተገናኘ ለዘገየ ክፍያ የሚጠየቀውን ወለድ
በሙሉ ወይም በከፊል እንዳይከፈል ሊፈቅድ ይችላል፡፡
• የዚህ አይነት የታክስ ዕዳ ምህረት ሊደረግ የሚችለው የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ በሚወሰን የገንዘብ
መጠን ልክ ይሆናል፡፡ በደንቡ አንቀጽ 7 መሰረት በዚህ ሁኔታ የሚሰጠው የታክስ እና የዘገየ ክፍያ ወለድ ምህረት ለሚንስትሩ
የተሰጠው የገንዘብ ጣሪያ 10,000,000/አስር ሚሊየን ብር/ ነው፡፡
• ሚኒስትሩ በዚህ መሠረት ምህረት የተሰጠበትን እያንዳንዱን የታክስ ዕዳ እና የወለድ መጠን እና ምህረት የተሰጠበትን
ምክንያት መዝግቦ በመያዝ በየስድስት ወሩ ለዋናው ኦዲተር ሪፖርት ማቅረብ አለበት፡ (ለግልፅነት እና ለቁጥጥር)
• የተጣሉ አስተዳደራዊ መቀጫዎች በመቀጫ አነሳስ መመሪያ 137/2010 መሰረት እና በእዳ ምህረት መመሪያ 64/2012 መሰረት
ይፈፀማሉ/ይነሳሉ
• በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ንብረታቸው ለወደመባቸው ባለሐብቶች ድጋፍ ስለሚደረግበት ሁኔታ የወጣ መመሪያ 69/2013
36
ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ …
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት /የገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ 88-93/
• በፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ከተከፋይ ሒሳብ ላይ በአዋጁ በተመለከተው የግብር ማስከፈያ መጣኔ መሰረት ተቀናሽ እየተደረጉ
ለግብር ባለስልጣኑ መከፈል ያለባቸው የግብር ዓይነቶችና ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ ገቢ
የማድረግ ግዴታ በህግ የተጣለባቸው ሰዎች በጸደቀው ቅጽ መሰረት ለባለስልጣኑ የማስታወቅና ግብሩን አብሮ የመክፈል ግዴታ
አለባቸው፤
ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን
ቀንሶ የማስቀረትና
ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ
ያለበት ሰው
1  ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር
 በሌላ ቀጣሪ ተቀናሽ ያልተደረገ ከአንድ
በላይ ቀጣሪዎች ባሉት ተቀጣሪ
ከሚከፈለው ጠቅላላ ክፍያ ላይ
የሚከፈል ግብር
በሰንጠረዠ “ሀ”
በተመለከተው
የማስከፈያ መጣኔ
መሰረት
 የተቀጣሪው ቀጣሪ
 ከተቀጣሪው ቀጣሪዎች
አንዱ ወይም ሌላው
(አስቀድሞ መረጃ ያገኘው)
37
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት …
ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈ
ያ መጣኔ
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው
2 በኢትዮጵያ ነዋሪ ባልሆኑ ሰዎች
ከሚፈጸም፣
 የወለድ ክፍያ
 የትርፍ ድርሻ ክፍያ
 የንዑስ ስራ ተቋራጭ ክፍያ
 የሮያልቲ ክፍያ
 የስራ አመራር ክፍያ
 የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ
 የመድን አርቦን ክፍያ (በውጭ አገር
ለሚኖሩ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች
የሚከፈል አርቦን)
 ወደውጭ የሚላክ ትርፍ
 በአዝናኝ የሚፈጸም ክፍያ
 ያልተከፋፈለ ትርፍ
10%
10%
10%
5%
15%
15%
5%
10%
10%
10%
- ወለድ የሚከፈለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት
- የትርፍ ድርሻ የሚያከፋፍለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ
ድርጅት
- ዋናው ስራ ተቋራጭ
- የሮያልቲ ክፍያ የሚፈጽመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ
ድርጀት
- የስራ አመራር ክፍያ የሚፈጽመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት
የሚሰራ ድርጀት
- የቴክኒክ ክፍያ የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ
ድርጀት (ያለው ነዋሪ ያልሆነ ሰው)
- የኢንሹራንስ አርቦን ክፍያ የሚፈጽም የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት
የሚሰራ ድርጀት
- ትርፍን ወደ ውጭ የሚልከው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ
ድርጀት
- ክፍያውን የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት (ያለው
ነዋሪ ያልሆነ ሰው)
- ያልተከፋፈለ ትርፍ ያለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው፡፡
38
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት …
ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ
መጣኔ
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና
ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው
3 የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም
በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት፤
 የትርድ ድርሻ ሲከፍል
 ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ
 ወለድ ሲከፍል
 ሮያልቲ ሲከፍል
10%
10%
10%
5%
- ክፍያውን የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነው ሰው
ወይም በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት
4 ነዋሪ የሆነ ድርጅት የኢትዮጵያ ነዋሪ ለሆነ
ሰው፡-
 የትርፍ ድርሻ ሲከፍል
 ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ
10%
- ክፍያ የፈጸመው ወይም ያልተከፋፈለ ትርፍ የያዘው
የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ድርጀት
5 በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም
በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት፡-
 ከዲፖዚት ወለድ ሲከፍል
 ከሌላ ምንጭ ወለድ ሲከፍል
 ወደውጭ ትርፍ ሲልክ
 ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ
5%
10%
10%
10%
- ክፍያን የፈጸመው ወይም ያልተከፋፈለ ትርፍ
የያዘው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም
በቋሚነት የሚሰራው ድርጀት
39
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት …
ተ.
ቁ
የግብር ዓይነት (የክፍያ
ዓይነት)
የማስከፈያ
መጣኔ
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ
የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው
6 በዕድል ሙከራ አሸናፊ
ለሆነ ማንኛውም ሰው
የሚፈጸም ክፍያ
15% - ክፍያ የሚፈጽመውና የዕድል ሙከራ ለማጫወት ፈቃድ ያለው
ሰው ወይም
- (ለአሸናፊው ገንዘቡን የሚከፈለው ሰው)
7 በአገር ውስጥ በሚደረጉ
ግብይቶች ከሚፈጸሙ
ክፍያዎች
 ከ10 ሺህ ብር በላይ
ለሆነ የዕቃ ሽያጭ
ከሚፈጸም ከፍያ
 ከ3000 ብር በላይ
የሆነ ማንኛውም
የአገልግሎት ክፍያ
ሲፈጸም
TIN ከቀረበ 2%
TIN ካልቀረበ
30%
- ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞችን ሳይጨምር ክፍያ የፈጸመ ማንኛውም
ድርጀት ፣ የመንግስት መስሪያ ቤት፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጀት
ወይም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጀት እንዲሁም ባለስልጣኑ
በሚያወጣው መመሪያ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ኃላፊነት
የተጣለባቸው ግለሰብ ግብር ከፋዮች፡፡
40
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት …
ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ
መጣኔ
ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና
ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው
8 በዓለም አቀፍ ድርጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ
ባለ የውጭ አገር ኢምባሲ፣ ዲፕሎማቲክ
ሚሽን ወይም ሌላ ኮንስለር ተቋም
ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ የሚፈጸም ክፍያ
 በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ
ድርጅት ለሌለውና የኢትዮጵያ ነዋሪ
ላልሆነ ሰው ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ
 በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ላልሆነ
ድርጀት ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ
የተከፈለ ክፍያ
በሰንጠረዥ
“ሀ” መሰረት
በሰንጠረዠ
“ሀ” መሰረት
በሰንጠረዠ
“ሀ” መሰረት
- ግብሩ በቀጣሪው ያልተከፈለ እንደሆነ
ክፍያ የተፈጸመበት ተቀጣሪ ራሱ ግብሩን
ቀንሶ በማስቀረት በየሶስት ወሩ ለታክስ
ባለስልጣኑ ማስገባት አለበት፡፡
- ተቀጣሪው ራሱ
- ተቀጣሪው ራሱ
41
“ግብር ለሥልጣኔ የሚከፈል ዋጋ ነው!”
አመሰግናለሁ!

Contenu connexe

Tendances

Benefits determination process
Benefits determination processBenefits determination process
Benefits determination processMonika Deswal
 
Public policy
Public policyPublic policy
Public policyhafsa317
 
Orgnization structure
Orgnization structureOrgnization structure
Orgnization structureMohamed Dahi
 
Best practice presented by berhanu tadesse
Best practice presented by berhanu tadesseBest practice presented by berhanu tadesse
Best practice presented by berhanu tadesseberhanu taye
 
Proclimation Presentation.pptx
Proclimation Presentation.pptxProclimation Presentation.pptx
Proclimation Presentation.pptxWoubshetNegussie1
 
Compensation management
Compensation managementCompensation management
Compensation managementProjects Kart
 
الدليل التطبيقي لمسير Masirh
الدليل التطبيقي لمسير Masirhالدليل التطبيقي لمسير Masirh
الدليل التطبيقي لمسير Masirhgh hai
 
Human Side of Mergers & Acquisitions
Human Side of Mergers & AcquisitionsHuman Side of Mergers & Acquisitions
Human Side of Mergers & AcquisitionsAchla Tyagi
 
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...HeythemHamdi
 
Introduction to Business Rescue Proceedings
Introduction to Business Rescue ProceedingsIntroduction to Business Rescue Proceedings
Introduction to Business Rescue ProceedingsCorne van Staden
 
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - Nepal
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - NepalRelationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - Nepal
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - NepalNitesh Khatiwada
 
التدريب.ppt
التدريب.pptالتدريب.ppt
التدريب.pptAhmedKayed6
 
Comparative Labor Relations
Comparative Labor RelationsComparative Labor Relations
Comparative Labor RelationsAnujith KR
 

Tendances (17)

Benefits determination process
Benefits determination processBenefits determination process
Benefits determination process
 
Public policy
Public policyPublic policy
Public policy
 
Labour laws in India
Labour laws in IndiaLabour laws in India
Labour laws in India
 
Orgnization structure
Orgnization structureOrgnization structure
Orgnization structure
 
Best practice presented by berhanu tadesse
Best practice presented by berhanu tadesseBest practice presented by berhanu tadesse
Best practice presented by berhanu tadesse
 
Proclimation Presentation.pptx
Proclimation Presentation.pptxProclimation Presentation.pptx
Proclimation Presentation.pptx
 
Performance based pay_ppt
Performance based pay_pptPerformance based pay_ppt
Performance based pay_ppt
 
Budgetary process
Budgetary processBudgetary process
Budgetary process
 
Compensation management
Compensation managementCompensation management
Compensation management
 
الدليل التطبيقي لمسير Masirh
الدليل التطبيقي لمسير Masirhالدليل التطبيقي لمسير Masirh
الدليل التطبيقي لمسير Masirh
 
Human Side of Mergers & Acquisitions
Human Side of Mergers & AcquisitionsHuman Side of Mergers & Acquisitions
Human Side of Mergers & Acquisitions
 
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...
مذكرة بعنوان مدونة سلوك و أخلاقيات العون العمومي بتونس لنيل درجة الماجستير في...
 
Introduction to Business Rescue Proceedings
Introduction to Business Rescue ProceedingsIntroduction to Business Rescue Proceedings
Introduction to Business Rescue Proceedings
 
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - Nepal
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - NepalRelationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - Nepal
Relationship Between Corporate Governance and Companies Act 2006 - Nepal
 
التدريب.ppt
التدريب.pptالتدريب.ppt
التدريب.ppt
 
Supplementary benefits
Supplementary benefitsSupplementary benefits
Supplementary benefits
 
Comparative Labor Relations
Comparative Labor RelationsComparative Labor Relations
Comparative Labor Relations
 

Similaire à Training Doc. for risk and compliance workers.pptx

Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk  employees.pptxTraining doc on income tax proc for Risk  employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptxhabeshagojam
 
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk  employees.pptxTraining doc on income tax proc for Risk  employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptxhabeshagojam
 
7. stump duty power point.pptx
7. stump duty power point.pptx7. stump duty power point.pptx
7. stump duty power point.pptxtagaye
 
____________________________________________.pptx.pdf
____________________________________________.pptx.pdf____________________________________________.pptx.pdf
____________________________________________.pptx.pdfHussenMahammed1
 
National Payment proclamation Draft.pdf
National Payment proclamation Draft.pdfNational Payment proclamation Draft.pdf
National Payment proclamation Draft.pdfAlemayehu
 

Similaire à Training Doc. for risk and compliance workers.pptx (7)

Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk  employees.pptxTraining doc on income tax proc for Risk  employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
 
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk  employees.pptxTraining doc on income tax proc for Risk  employees.pptx
Training doc on income tax proc for Risk employees.pptx
 
7. stump duty power point.pptx
7. stump duty power point.pptx7. stump duty power point.pptx
7. stump duty power point.pptx
 
____________________________________________.pptx.pdf
____________________________________________.pptx.pdf____________________________________________.pptx.pdf
____________________________________________.pptx.pdf
 
National Payment proclamation Draft.pdf
National Payment proclamation Draft.pdfNational Payment proclamation Draft.pdf
National Payment proclamation Draft.pdf
 
Amharic version income tax
Amharic version income taxAmharic version income tax
Amharic version income tax
 
eater of eater
eater of eatereater of eater
eater of eater
 

Training Doc. for risk and compliance workers.pptx

  • 1. ግዴታዬን እወጣለሁ መብቴን እጠይቃለሁ! ማህሌት አምዴ ጥቅምት/2015 ዓ.ም አዲስ አበባ የታክስ ምንነትና ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ ኃላፊነት ከህግ ተገዢነትና ታክስ አስተዳደር አንፃር ለሰራተኞች የተዘጋጀ
  • 2. 2 የሰነዱ ይዘት 01 መግቢያ 02 የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እና ጠቅላላ መረጃ 03 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ ኃላፊነት
  • 3. 3 • ክፍል አንድ - መግቢያ • አጠቃላይ የታክስ አስተዳደር መርህ ላይ ግልጽነትን ለመፍጠር ፤ • የህግ ተገዢነት በተጨባጭ ከታክስ ኦፕሬሽን አንፃር ምን ይመስላል የሚለውን ግንዛቤ ለማስጨበጥ፤ • ህጉን ተረድቶ የሚመለከታቸው አካላት ግዴታቸውንና ኃላፊነታቸውን በቀላሉ እንዲወጡ ለማስቻል፤ የሥልጠናው ዓላማ እና የገቢ ሰብሣቢ ተቋማት ዓላማ • ከግብር/ታክስ/ እና ከተለያዩ ቀረጦች የሚገኝ የመንግስት ገቢን መሰብሰብ፣ • ሕጋዊ የሆነውን የንግድ እንቅስቃሴን ማሣለጥ፣ • የማህበረሰቡን ደህንነት መጠበቅ እና • ፍትሐዊ የሐብት ክፍፍል እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡ የሥልጠናው ዓላማ የገቢ ሰብሣቢ ተቋማት በዋነኝነት የመቋቋማቸው ዓላማ
  • 4. 4 • ገቢ ባገኘ ሰው ላይ ብቻ ግብር መጣል (tax only income) ፤ በጣም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ከግብር ነጻ ማድረግ ፤ ገቢው እያደገ ሲሄድ እየጨመረ በሚሄድ የግብር ማስከፈያ መጣኔ ግብር ማስከፈል (progressivity/ ዋና የታክስ አስተዳደር መርሆች/Principles of taxation/ - የታክስ አጣጣልንና የታክስ ህግና ሥርዓት አወቃቀርን በተመለከተ ምን ሁኔታዎችን ማሟላት እንዳለበት ከሞላ ጐደል በዓለም ላይ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያገኙ የታክስ ህግና ሥርዓት መሠረቶች የታክስ መሠረታዊ መርሆዎች በመባል ይታወቃሉ • ለአንድ ዓይነት ግብር አንድ ዓይነት የግብር መጣኔ መጠቀም ፤ወጥ በሆነ የማስከፈያ መጣኔ ግብር ማስከፈል ፤ ከገቢው መጠን ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የግብር መጠን ማስከፈል (proportionality of tax to income) • በሁሉም ግብር ከፋዮች ላይ የሚያርፈው የግብር ጫና እኩል ወይም ተመጣጣኝ እንዲሆን ማድረግ (proportional equality of tax burden) ፤ግብር የመክፈል አቅም ያለው ሁሉ እንደየአቅሙ ግብር እንዲከፍል ማድረግ (equitable contribution to the national revenue)፤በግብር ምንም ዓይነት ልዩነት አለማድርግ (tax without discrimination)፤ • መሰረታዊ የታክስ ህግ መርሆዎችና ደንቦች በአዋጅ መደንገግና ለረጅም ጊዜ ቋሚ ሆነው የሚቀጥሉ መሆን አለባቸው ፤ መለስተኛ ክብደት ያላቸው ጉዳዮች ደግሞ በመለስተኛ ህጎች (regulations) መደንገግ አለባቸው፡ ለመመሪያና ለባለስልጣን ውሳኔ የሚተው ጉዳዮች የግብር ከፋዮን መሰረታዊ መብቶች የማይነኩና አነስተኛ ሥነ ሥርዓታዊ ጉዳዮች ብቻ መሆን አለባቸው፡፡ ክፍል ሁለት የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እና ጠቅላላ መረጃ የመክፈል አቅም (Ability to pay) ተመጣጣኝነት (fairness) ፍትሃዊነት (equitability) ተገማችነት (predictability)
  • 5. 5 • ህጉ ተቃርኖ የማይታይበትና ከዳር እስከዳር የሚጣጣምና ወጥ መሆን አለበት፡ • በተፃፈ ህግ የሚመራ እና ለድርድር ክፍት ያልሆነ መሆን አለበት፡ ዋና የታክስ አስተዳደር መርሆች… • አቅም በፈቀደ መልኩ የታክስ አስተዳደር እና የታክስ ህግ ተገዢነት ወጪ በጣም አነስተኛ እና በአጭር ጊዜ የሚከወን መሆን አለበት፡ • ህጉ ለግብር ከፋዩ ጭምር ግልጽና ለመረዳት የሚያመች እንዲሁም ለአሰራር ቀላል መሆን አለበት፡ • የታክስ ስርዓቱ ተጨማሪ ኢንቨስትመንትን /የንግድ ስራ እንቅስቃሴን/ የሚገታ መሆን የለበትም የዘመናዊ ታክስ አስተዳደር መርህ እናጠቅላላ መረጃ የቀጠለ… ወጥነት (consistency) በቅልጥፍና /በብቃት (Efficiency principle) ግልጽነትና አመቺነት (clarity simplicity) ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ (Investment or productivity Principle)
  • 6. 6 • የቀጠለ… አጠቃላይ መረጃ • ሕግ የሰውን ልጅ ባህሪ፣ እንቅስቃሴና ግንኙነት መልክና ሥርዓት ለማስያዝ ፖለቲካዊ አደረጃጀት ባለው ህብረተሰብ ውስጥ ስልታዊ በሆነ መልኩ ኃይል መጠቀምን የሚፈቅድ ሥርዓት ነው፡፡ • የፍርድና የአስተዳደር ውሳኔዎች ፍሰት፣ህጋዊ እርምጃዎችና የህግ ውሳኔ ሂደቶችን የያዘ ነው፣ የታክስ አስተዳደር በተፃፈ ህግ ከላይ የተመለከቱትን መርሆች ተከትሎ እንዲመራ የሚጠበቅ ስርዓት ነው • የታክስ ህግ መንግስት (state) ሰዎች ወይም ድርጅቶች የሚከፍሉትን የታክስ ዓይነት፣የማስከፈያ ምጣኔ፣የታክስ አወሳሰኑን፣አሰባሰቡን በአጠቃላይ ታክስ የመክፈል ግዴታንና የግዴታቸውን አፈፃፀም አስመልክቶ አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ በጽሁፍ የሚያውጀው የታክስ አስተዳደርና የአሠራር ሥርዓቱ መሠረታዊ መርሆዎች የሚገለጹበት የህግ ሰነድ ነው፡፡ የህግ ምንነት የታክስ ህግ ምንነት
  • 7. 7 አጠቃላይ መረጃ … ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣን (taxing power) • ከታክስ የሚሰበሰብ ገቢ ለአንድ መንግስት ህልውና እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣን ለመንግስት ብቻ የተሰጠ ሥልጣን ነው፡፡ ለግለሰብ ወይም ለሌላ አካል የዚህ ዓይነት ሥልጣን በየትኛውም ዓለም አልተሰጠም፡፡ • በኢትዮጵያ መንግስት (state) ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣኑን የሚያገኘው ከህገ መንግስቱ አንቀጽ 96፣97፣ 98 እና 99 ነው፡፡ • የህገ መንግስቱ አንቀጽ 96 የፌደራል መንግስትን መሠረታዊ የታክስና የግብር ሥልጣን የሚደነግግ ሲሆን • አንቀጽ 97 የክልል መንግስታት የታክስ አስተዳዳር ስልጣንን ያሣያል • አንቀጽ 98 ደግሞ የክልልና የፌደራል መንግስታት የጋራ የታክስና የግብር ሥልጣንን ይወስናል፡፡ አንቀጽ 99 በህግ በግልጽ ለፌደራል መንግስት ወይም ለክልል መንግስታት ወይም ለሁለቱም በጋራ ያልተሰጠ የታክስና የግብር ሥልጣን በፌዴሬሽንና በህዝብ ተወካዮች ምከር ቤቶች የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምጽ የታክስ ሥልጣኑ ለፌደራል መንግስት፣ ለክልሎች ወይም ለሁለቱም የጋራ ሥልጣን እንዲሆን ይወስናል፡፡
  • 8. 8 • የታክስ ሥርዓት የምንለው የታክስ ህጉንና ይህን የታክስ ህግ መሠረት በማድረግ በየደረጃው የሚወጡ መመሪያዎችና የአሠራር ሥርዓቶች በታክስ ባለሥልጣኑ የሚዘረጉ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ፣ የኦዲት ሥርዓቱንና የመረጃ አስተዳደር ሥርዓቱን ጨምሮ የአገልግሎት አሰጣጡንና የቅሬት አፈታት ሥርዓቱን በማጠቃለል “የታክስ አስተዳደር ሥርዓት” ብለን የምንጠራውን አስተዳደራዊ ሥርዓት የሚወክል መሠረታዊ ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡ የታክስ ሥርዓት ምንነት  ግሎባል (aggregated) የታክስ ሥርዓት  ስኬጁላር (disaggregated) የታክስ ሥርዓት ተብለው የሚታወቁ ናቸው፡፡ • ግሎባል የታክስ ሥርዓት - ግብር ከፋዩ የሚያገኘውን ማንኛውንም ዓይነት ገቢ በአንድ ላይ በመደመር በአንድ የግብር ማስከፈያ ምጣኔ ግብር እንዲከፍል የሚደረግበት ሥርዓት ነው፡ • ስኬጁላር የታክስ ሥርዓት የሚባለው አንድ ግብር ከፋይ የሚያገኛቸውን ገቢዎች እንደየገቢው ዓይነት በመከፋፈል ወይም በመመደብ ለእያንዳንዱ የገቢ ዓይነት በስኬጁል የተቀመጡ የግብር ማስከፈያ ምጣኔዎችን በመጠቀም የተለያየ ግብር በመወሰን የተለያዩ የህግ መርሆዎችንና መሪ ድንጋጌዎች ተጠቅሞ ታክሱን የሚሰበስብበት ሥርዓት ነው፡፡ • የኢትዮጵያ የታክስ ሥርዓት ይህንን ዓይነት የታክስ ሥርዓት የሚከተል ነው አጠቃላይ መረጃ … የታክስ ሥርዓት የታክስ ሥርዓት ዓይነቶች/Types of Taxing System/ ግሎባል (aggregated) የታክስ ሥርዓት ስኬጁላር (disaggregated) የታክስ ሥርዓት
  • 9. 9 አጠቃላይ መረጃ …  የገቢ ሠንጠረዦች(Schedules of Income) /አንቀጽ 8/ • በገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 አምስት የግብር ሠንጠረዦች ይፋ ተደርገዋል፡- ሠንጠረዥ ሀ - ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ (income from employment) ሠንጠረዥ ለ - ከቤት ኪራይ የሚገኝ ገቢ (income from rental of building) ሠንጠዥ ሐ - ከንግድ ሥራ የሚገኝ ገቢ (income from Business) ሠንጠረዥ መ- ሌሎች ገቢዎች (other income) ሠንጠረዥ ሠ - ከግብር ነፃ የሆኑ ገቢዎች (exempt income) • በአንድ ሠንጠረዥ ውስጥ የሚወድቁ የተለያዩ ገቢዎችን ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ያገኘ ሰው ሁሉም ገቢዎች ተጣምረው በዚያው ሠንጠረዥ ሥር ግብር ይከፈልባቸዋል፡፡
  • 10. 10 አጠቃላይ መረጃ …  የተፈፃሚነት ወሰን /አንቀጽ 7/ የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 የህግ አንቀጽ የተደነገገው የኢትዮጵያ መንግስት ያለውንና ሊኖረው የሚገባውን የግብር ሥልጣን (Tax jurisdiction) መሠረት በማድረግ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት አዋጁ - የኢትዮጵያ ነዋሪ በሆኑ ሰዎች ላይ በዓለም ዙሪያ በሚያገኙት ገቢ ላይ ግብር እንዲከፍሉ፣ - የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆኑት ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ባገኙት ገቢ ላይ ወይም የኢትዮጵያ ምንጭ በሆነ ገቢ ላይ ብቻ ግብር እንዲከፍሉ ደንግጓል፡፡
  • 11. 11 • አጠቃላይ መረጃ … የሚከተሉት የኢትዮጵያ ነዋሪዎች ናቸው፡- - ነዋሪ የሆነ ግለሰብ  ኢትዮጵያ ውስጥ ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ (domicile) ያለው፣  በመንግስት ተመድቦ በውጭ አገር የሚሠራ ኢትዮጵያዊ ዜጋ፣  በኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በተከታታይ ሳያቋርጥ ወይም በመመላለስ ከ183 ቀናት በላይ የኖረ ግለሰብ፣ - ነዋሪ የሆነ ድርጅት  ኢትዮጵያ ውስጥ የተቋቋመ /የተመሠረተ/፣  ወሳኝ የሆነ የሥራ አመራር የሚሰጥበት ሥፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው፣ የፌደራል መንግስት፣ የክልል መንግስታትና ከተማ አስተዳደሮች፣ የተፈፃሚነት ወሰን የሚከተሉት ገቢዎች ከኢትዮጵያ የመነጩ ናቸው፡ • በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከናወን የቅጥር አገልግሎት የተገኘ ገቢ - ክፍያው የሚፈፀምበት ሥፍራ የትም ቢሆን፣ - ውሉ የተፈረመው የትም ቢሆን፣ - የአሠሪው ነዋሪነት የትም ቢሆን፣ - ሠራተኛው የኢትዮጵያ ነዋሪ ቢሆንም ባይሆንም፣ • በኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት፣በክልል መንግስታት ወይም በከተማ አስተዳደሮችና በእነዚህ ስም ለቀጣሪው የተፈፀመ ክፍያ - የቅጥር አገልግሎቱ የትም ቢከናወን፣ • በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያገኘው የግድ ሥራ ገቢ፣ ነዋሪነት የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 አንቀጽ 5 የገቢ ምንጭ የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 አንቀጽ 6
  • 12. 12 • የተፈፃሚነት ወሰን… - በቋሚነት በሚሠራ ድርጅት አማካኝነት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራ የሚያገኘው ገቢ፣ - በቋሚነት የሚሠራው ድርጅት ከሚያስተላልፏቸው ዕቃዎች ወይም ሸቀጦች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሣሣይ የሆኑ ዕቃዎችን ወይም ሸቀጦችን ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጥታ በማስተላለፍ የሚያገኘው ገቢ፣ - በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት ከሚያከናውናቸው ማናቸውም የንግድ ሥራዎች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሣሣይ የሆኑ ሌሎች የንግድ ሥራ እንቅስቃሴዎችን ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጥታ በማከናወን የሚያገኘው ገቢ፣ የገቢ ምንጭ… - በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ድርጅት የሚከፍለው የትርፍ ድርሻ፣ - የማይንቀሳቀስ ሃብትና በኢትዮጵያ የሚገኝን የሚንቀሳቀስ ሃብት በማከራየት የሚገኝ ገቢ፣ - በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝን የማይንቀሳቀስ ሃብት በማስተላለፍ ወይም ግንኙነት ባላቸው ሰዎች የተያዘንና ከዋጋው 5ዐ% በላይ የሆነን የማይንቀሳቀስ ሃብት ጥቅም በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ፣ - በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ኩባንያ ያወጣው (የሚሸጠው) አክሲዮን ወይም ቦንድ፣ - በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኝ መድን ለተገባለት የአደጋ ሥጋት የሚከፈል የመድን አርቦን፣ - በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከናወን የመዝናኛ ወይም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚገኝ ገቢ፣ - በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄድን የዕድል ሙከራ በማሸነፍ የሚገኝ ገቢ፣ - የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው የኢትዮጵያ ነዋሪ ከሆነ ሰው የሚያገኘው የወለድ ገቢ፣ - የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው የኢትዮጵያ ነዋሪ ከሆነ ሰው የሚያገኘው የሮያልቲ ክፍያ ገቢ፣ - የኢትዮጵያ ነዋሪ ለሌላ የኢትዮጵያ ነዋሪ የሚከፍለው የወለድ እና የሮያልቲ ክፍያ ገቢ፣ - የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት የኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው የሚከፍሉት የሥራ አመራር ወይም የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ያልሆነ ሰው፣ የሚከተሉት ገቢዎች ኢትዬጽያ ውስጥ የመነጩ ገቢዎች ይባላሉ /አ6 ንአ 4/
  • 13. 13 ክፍል ሶስት ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ ሚና /ኃላፊነት/ •በየትኛውም የታክስ አስተዳደር ስርዓት የግብር ከፋዮች መሰረታዊ ግዴታዎች በ 4 ዋና ዋና ነጥቦች ይለካሉ፡- 1. ለግብር ከፋይነት መመዝገብ (Register):- የጣት አሻራ መስጠት፣ መለያ ቁጥር ማውጣት፣ ለተ.እ.ታ መመዝገብ፤ ለኤክሳይዝ ታክስ ፤እና ልዩ ልዩ ለውጦችን ማስታወቅ፤ 2. ማስታወቅ (Filing):- የሥራ ግብር፣ የቤት ኪራይ ገቢ፣ የትርፍ ግብር ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የኤክሳይዝ ታክስ ወ.ዘ.ተ ማሣወቂያዎች በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ማስታወቅ፤ 3. ሪፖርት ማድረግ (Reporting):- ትክክለኛ መረጃ /ከዲክላሬሽን ጋር በተያያዘ የመስጠት ግዴታ፤ 4. ታክስ/ግብር መክፈል (Payment):- የታክስ/ግብር ግዴታዎችን በፈቃደኝነት በትክክለኛው መንገድ የመወጣት ሁኔታና በትክክለኛው ሰዓት በወቅቱ መክፈል፤
  • 14. 14 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ስለምዝገባ (የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀጽ 9 - 11) ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ •አስቀድሞ የተመዘገበ ካልሆነ በስተቀር በታክስ ሕግ መሠረት ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ሰው በባለሥልጣኑ ዘንድ ለመመዝገብ ማመልከት አለበት፡፡ •ነገር ግን ይህ ድንጋጌ፡- በኢትዮጵያ የሚያገኘው ገቢ ብቻ በገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ 51 መሰረት በኢትዬጲያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው የትርፍ ድርሻ፣ ሮያሊቲ፣ ወለድ፣ የስራ አመራር ክፍያ ፣ የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ ወይም የመድን አረቦን ከኢትዬጲያ ውስጥ ያገኘን ሰው እና አንቀጽ 53 መሰረት በኢትዬጲያ ነዋሪ ያልሆኑ የመዝናኛ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም እንዲሁም በሠንጠረዠ “መ” መሰረት የሚጣለው የመጨረሻ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ብቻ ያለው ግለሰብ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
  • 15. 15 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ … ለምዝገባ - ባለሥልጣኑ ባጸደቀው ቅጽ መሠረት ማመልከቻ መቅረብ ይኖርበታል፡- “የጸደቀ ቅጽ” ማለት በዚህ አዋጅ አንቀጽ 79 የተሰጠው ትርጉም ይኖረዋል፤ የአዋጁን አንቀጽ 79 ስንመለከት፡ በታክስ ከፋይ የሚቀርብ ማንኛውም የታክስ ማስታወቂያ፣ ማመልከቻ፣ ማስታወቂያ፣መግለጫ ወይም ሌላ ሰነድ በፀደቀው ቅጽ መሠረት እንደቀረበ የሚቆጠረው ሰነዱ፡- የሰነዱ ዓይነት በባለሥልጣኑ በፀደቀ ቅጽ መሠረት የቀረበ፣ ማንኛውንም ተያያዥ ሰነዶች ጨምሮ ቅጹ የሚጠይቀውን መረጃ የያዘ፣ እና ቅጹ በሚጠይቀው መሠረት የተፈረመ፣ ሲሆን ነው፡፡ • የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ በሚወሰነው መሠረት የጣት አሻራ መለያን ጨምሮ የግለሰቡን ማንነት ከሚያረጋግጥ የሰነድ ማስረጃ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፤ በፌደራል የታክስ አስተዳደር ደንብ ቁጥር 407/2009 አንቀጽ 4 መሰረት ከሚከተሉት አንዱን የማንነት የሰነድ ማስረጃ ከሚያቀርበው ማመልከቻ ጋር ያቀርባል፡- ወቅታዊ የግለሰቡ የነዋሪነት መታወቂያ ወይም የኢትዬጽያ/የሌላ ሀገር/ ፖስፖርት ገጽ የተረጋገጠ ቅጂ ወይም ፣ የመንጃ ፈቃድ ቅጂ፣ ወይም የግለሰቡ የተረጋገጠ የልደት የምስክር ወረቀት ቅጂ ወይም ባለስልጣኑ አስፈላጊ መስሎ የሚታየውን ሌላ ማንኛውንም ማስረጃ እንዲያቀርብለት ሊጠይቀው ይችላል፡፡ ኩባንያ በሚሆንበት ጊዜ ኩባንያው የተቋቋመበትን ወይም የተመዘገበበትን የምስክር ወረቀት ከማመልከቻው ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡ • ታክስ ከፋዩ ለታክስ የመመዝገብ ግዴታ ካለበት ቀን አንስቶ በ21 ቀናት ውስጥ ወይም ባለሥልጣኑ በፈቀደው ተጨማሪ ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፡፡ • ባለሥልጣኑ ለመመዝገብ ያመለከተው ሰው በታክስ ሕግ መሠረት ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት መሆኑን ሲያምንበት ይመዘግበዋል፤ የምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ ይሰጠዋል፡፡
  • 16. 16 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ታክስ ከፋዮችን ስለመመዝገብ … • ነገር ግን አንድ ሰው ለመመዝገብ ሲያመለክት ያቀረበውን ማስረጃ ይህ ሰው ተጨማሪ የምዝገባ ማመልከቻ ቅጽ ማቅረብ ሳያስፈልገው ባለሥልጣኑ ማስረጃውን ይህ ሰው በሌላ የታክስ ሕግ ለአንድ የተለየ ታክስ እንዲመዘገብ ያለበትን ግዴታ ወይም ለመመዝገብ የተሰጠውን ፈቃድ ለማሟላት ሊጠቀምበት ይችላል፡ • ይህ ቢኖርም ባለሥልጣኑ የአንድን ሰው ተጨማሪ ምዝገባ በተሟላ ሁኔታ ለማከናወን የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ሌላ ተጨማሪ መረጃ ያቀርብ ዘንድ ይህንን ሰው ሊጠይቀው ይችላል፡ • መመዝገብ ሲኖርበት ያልተመዘገበን ሰው ባለሥልጣኑ በፀደቀው ቅጽ መሠረት መዝግቦ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ሊሰጠው ይችላል፡፡ • የአንድ ሰው ምዝገባ ተፈፃሚ የሚሆነው የዚህን ሰው ምዝገባ በሚያረጋግጠው የምስክር ወረቀት ላይ ከተመለከተው ቀን ጀምሮ ነው፡፡ • በአዋጁ መሰረት መመዝገብ ሲገባው ያልተመዘገበ እንደሆነ መመዝገብ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ እስከተመዘገበበት ጊዜ ታሣቢ ተደርጐ በአዋጁ አንቀጽ 101 ፡- • በታክስ ከፋይነት ያልተመዘገበ እንደሆነ የግብሩን 25% መቀጮ ይቀጣል፡፡ • የሚከፈል ግብር ከሌለ በየወሩ 1,000 ብር ይቀጣል
  • 17. 17 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ምዝገባን ስለመሰረዝ • እንዲሰረዝለት ለባለስልጣኑ ማመልከት አለበት፣ • ምዝገባን ለማሰረዝ የሚቀርበው ማመልከቻ በፀደቀው ቅጽ መሠረት፣ እና የተመዘገበው ሰው በሁሉም የታክስ ሕጐች የተጣለበት የመመዝገብ ግዴታ ከተቋረጠበት ቀን አንስቶ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ወይም ባለሥልጣኑ በሚሰጠው ተጨማሪ ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፡፡ • አንድ ሰው በዚህ መሰረት ለመሰረዝ ማመልከቻ ካቀረበ በሌላ የታክስ ሕግ ለአንድ የተለየ ታክስ የተደረገው ምዝገባ እንዲሰረዝለት ጭምር እንዳመለከተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ • አንድ ሰው በዚህ መሠረት ማመልከቻ ሲያቀርብ ባለሥልጣኑ ይህ ሰው ሥራውን ያቆመ መሆኑንና በሁሉም የታክስ ሕጎች የመመዝገብ ግዴታ የሌለበት መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ ለዚህ ሰው የጽሑፍ ማስታወቂያ በመስጠት ምዝገባውን ይሰርዘዋል፡፡ • ምዝገባ የተሠረዘ መሆኑን የሚገልፀው ማስታወቂያ ማመልከቻው ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ለአመልካቹ መሰጠት የሚኖርበት ሲሆን፣ ባለሥልጣኑም የምዝገባ ይሰረዝልኝ ማመልከቻው ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 90 ቀናት ውስጥ የታክስ ከፋዩን የታክስ ጉዳዮች በተመለከተ የመጨረሻ ኦዲት ሊያደርግ ይችላል፡ • አንድ ሰው ምዝገባ እንዲሰረዝለት ጥያቄ ያላቀረበ እንደሆነ ባለሥልጣኑ ይህ ሰው ሥራውን ሙሉ በሙሉ ማቆሙን እና ለታክስ ሕጐች ዓላማ የመመዝገብ ግዴታ የሌለበት መሆኑን እንዲሁም የተፈጥሮ ሰው ከሆነ መሞቱን፣ ኩባንያ ከሆነም መፍረሱን፣ ወይም ሌላ ማንኛውም ሰው ሕልውናው የተቋረጠ መሆኑን ሲያምንበት ለታክስ ከፋዩ ወይም ለታክስ እንደራሴው የጽሑፍ ማስታወቂያ በመስጠት ምዝገባውን ይሰርዛል፡ • ሆኖም የአንድ ሰው የምዝገባ መሰረዝ በሌላ ታክስ ሕግ አንድን የተለየ ታክስ የሚመለከት ሲሆን፣ በዚያ የታክስ ሕግ ምዝገባ መሰረዝን በሚመለከት የሠፈሩትን ግዴታዎች ማሟላት ግዴታ ይሆናል፡፡ • ከግብር ከፋይነት እንዲሰረዝ ያልጠየቀ በየወሩ 1,000 ብር መቀጫ ይከፍላል (አንቀጽ 101 ን.አ 4)
  • 18. 18 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … • ስለታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008አንቀጽ 12 - 15) ታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር • ታክስ ከፋዮችን ለመለየት እንዲቻል ባለሥልጣኑ ለታክስ ሕጐች ዓላማ ሲባል ለተመዘገበ ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር በሚል የሚታወቅ ቁጥር ይሰጣል፤ ታክስ ከፋዩም የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን የታክስ ሕጎች በሚያዙት መሠረት መጠቀም አለበት፡፡ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ስለመሰጠት • ለሁሉም የታክስ ሕጐች አንድ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የሚሰጥ ሲሆን አንድ ታክስ ከፋይ በማንኛውም ጊዜ አንድ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ብቻ ይኖረዋል፡፡ • ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የታክስ መለያ ቁጥር የሚሰጠው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ማስታወቂያ በመስጠት ይሆናል፡ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር አጠቃቀም • የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የተሰጠው ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን በማንኛውም የታክስ ማስታወቂያ፣ ማስታወቂያ ወይም ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል በሚቀርብ ወይም ጥቅም ላይ በሚውል ሰነድ ወይም በታክስ ሕግ መሠረት በሚዘጋጅ ሰነድ ላይ መግለጽ ይኖርበታል፤ • የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ለተሰጠው ሰው ብቻ የሚያገለግል ስለሆነ በሌላ ሰው ጥቅም ላይ ሊውል አይገባም፤ • የዚህ አዋጅ አንቀጽ 103 ከታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ጋር የተገናኘ ቅጣቶችን አስቀምጧል፡፡
  • 19. 19 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ለውጦችን ስለማሳወቅ • ማንኛውም የተመዘገበ ሰው ስሙ፣ ቋሚ አድራሻው ወይም የፖስታ አድራሻው፣ የተቋቋመበት መተዳደሪያ ደንብ ወይም ዋንኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም እንቅስቃሴዎቹ ከተለወጡ ከባለሥልጣኑ ጋር ግንኙነት የሚያደርግበት የባንክ አድራሻ፣ የኤሌክትሮኒክ አድራሻ ከተለወጠ ባለሥልጣኑ በመመሪያ የሚወሰናቸው ሌሎች ዝርዝሮች በተመለከተ ፣ ለውጥ ሲከሰት ለውጡ በተከሰተ በ30 ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፤ የተመዘገበ ሰው የለውጥ ማስታወቂያ ሲያቀርብ ይህ ሰው በሌላ የታክስ ሕግ ለአንድ ለተለየ ታክስ ካደረገው ምዝገባ ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ለውጦችን ማስታወቅን በተመለከተ የተጣለበትን የማስታወቅ ግዴታ እንደተወጣ ይቆጠራል፡፡ ይህን ያልተወጣ • በንግድ ሥራው ላይ ማንኛውንም ለውጥ ያላሳወቀ ብር 2ዐ,ዐዐዐ፣ የዚህ አዋጅ አንቀጽ 114 ን.አ 1 • የመመስረቻ ጽሁፍ (የመተዳደሪያ ደንብ) ወይም የነዚህን ማሻሻያዎች ያላቀረበ ላላቀረበበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም ለወሩ ከፊል ብር 1ዐ,ዐዐዐ ቅጣት ይከፍላል ፣ አንቀጽ 114 ን.አ 2
  • 20. 20 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … የታክስ ማስታወቂያዎችን ስለማቅረብ (የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 21 – 24) ይህንን አንቀጽ ተፈፃሚ የምናደርገው በገቢ ግብር አዋጁ አንቀጽ 83 ላይ በተቀመጠው ግብርን የማሣወቅ ጊዜ መነሻ በማድረግ ነው፡፡ (በገቢ ግብር አዋጁ አንቀጽ 83 መሰረት ደረጃ “ሀ” የግብር ዓመቱ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት የአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ፣የደረጃ “ለ” የግብር ዓመቱ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ፣ የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋይ ለእያንዳንዱ በጀት ዓመት ከሀምሌ 1 ቀን እስከ ሐምሌ 30 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ እንዲሁም ወርሃዊ ታክሶች በቀጣዩ ወር የግብሩን/የታክስ ማስታወቂያውን ማ ይኖርበታል፡፡) • በታክስ ሕግ የታክስ ማስታወቂያ የማቅረብ ግዴታ የተጣለበት ሰው ማስታወቂያውን በፀደቀው ቅጽ እና በዚህ አዋጅ መሠረት በሚወጣ ደንብ በተመለከተው አኳሃን ማቅረብ አለበት፤  በታክስ አስተዳደር ደንብ ቁጥር 407/2009 አንቀጽ 8 መሰረት በሌላ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር በኤሌክትሮኒክ ዘዴ በማስተላለፍ ወይም ባለስልጣኑ የሚሰጠውን መመሪያ በመከተል ወይም በሌላ ማናቸውም ሁኔታ በአካል በመቅረብ ወይም በፓስታ ለባለስልጣኑ በመላክ • ቀደም ሲል የቀረበው የታክስ ማስታወቂያ በታክስ ከፋዩ የተዘጋጀ የራስ ታክስ ማስታወቂያ ካልሆነ በስተቀር ማንኛውም ታክስ ከፋይ ባለሥልጣኑ በሚሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ፡- 1/ አስቀድሞ ለባለሥልጣኑ ያቀረበውን የታክስ ማስታወቂያ የሚያሟላ የታክስ ማስታወቂያ፣ ወይም 2/ ባለሥልጣኑ በሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ የተመለከቱ መረጃዎችን የያዘ የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ አለበት፡፡
  • 21. 21 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … የታክስ ማስታወቂያዎችን ስለማቅረብ… • ባለሥልጣኑ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም በቀረበ የታክስ ማስታወቂያ አይገደድም፡፡ ስለሆነም ባለሥልጣኑ ባገኘው ማንኛውም አስተማማኝ እና ሊረጋገጥ የሚችል መረጃ ላይ በመመሥረት ታክስ ከፋዩ መክፈል ያለበትን የታክስ መጠን ሊወስን ይችላል፡፡ • የኤሌክትሮኒክስ የታክስ ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ታክስ ከፋይ በሚያቀርበው የታክስ ማስታወቂያ ላይ መፈረም የሚኖርበት ሲሆን የታክስ ማስታወቂያውም፣ ማስታወቂያው እና ተያያዥ ሰነዶችም የተሟሉና ትክክለኛ መሆናቸውን ታክስ ከፋዩ የሚያረጋግጥበትን መግለጫ መያዝ አለበት፡፡ • የውክልና ሥልጣን በህግ አግባብ የተሰጠው ከሆነ የታክስ ከፋዩ የታክስ ወኪል ወይም የታክስ እንደራሴው የታክስ ማስታወቂያውን ሊፈርም እና የማረጋገጫ መግለጫ ሊሰጥ ይችላል፡፡ • የታክስ ማስታወቂያው በታክስ ከፋዩ የታክስ ወኪል ወይም በታክስ እንደራሴው የተፈረመ ሲሆን ታክስ ከፋዩ የማስታወቂያውን ይዘት እንደሚያውቅ እና ስለማስታወቂያው የተሟላ እና ትክክለኛ ስለመሆኑ ማረጋገጫ እንደሰጠ ይቆጠራል፡፡ • የታክስ ማስታወቂያ በወቅቱ ሣይቀርብ ቢቀር የዚህ አዋጅ አንቀጽ 104 ላይ የታክስ ማስታወቂያ ዘግይቶ ማቅረብ ስለሚያስከትለው ቅጣት ተደንግጓል፡፡
  • 22. 22 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … የታክስ ማስታወቂያዎች አስቀድሞ ስለማቅረብ • ሥራውን ያቋረጠ ማንኛውም ታክስ ከፋይ ሥራውን ያቋረጠ መሆኑን ሥራውን ካቆመበት ቀን ጀምሮ በ30 (ሰላሳ) ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሑፍ ማሳወቅ አለበት፡፡ • ይህ የሚመለከተው ታክስ ከፋይ ሥራውን ባቆመ በ60 (ስልሳ) ቀናት ውስጥ ወይም ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ በሚሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ በሚወስነው ከዚያ ባነሰ ጊዜ ውሰጥ፡ ታክስ ከፋዩ ሥራውን ላቆመበት የታክስ ጊዜ ወይም የታክስ ማስታወቂያ ጊዜው ላልደረሰ ከዚያ በፊት ለነበረ የታክስ ጊዜ የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ፣ እና በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው መሠረት ሊከፈል የሚገባውን ታክስ መክፈል አለበት፡፡ • ማንኛውም ታክስ ከፋይ ከኢትዮጵያ ሊወጣ ከሆነና የታክስ ከፋዩ ከኢትዮጵያ መውጣት በጊዜያዊነት አለመሆኑ የሚገመት ከሆነ ታክስ ከፋዩ ከኢትዮጵያ ከመውጣቱ በፊት፡ የወቅቱን የታክስ ማስታወቂያ እና ከኢትዮጵያ በሚወጣበት ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ የማቅረቢያ ጊዜው ላልደረሰው ከዚያ በፊት ለነበረው የታክስ ጊዜ የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ፣ እና በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው መሠረት መከፈል የሚገባውን ታክስ መክፈል ወይም ታክሱ የሚከፈልበትን ሁኔታ ለባለሥልጣኑ አጥጋቢ በሆነ አኳሃን ማመቻቸት፣አለበት፡፡ • በማንኛውም የታክስ ጊዜ ታክስ ከፋዩ የታክስ ጊዜውን የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ በሚገባው ጊዜ አያቀርብም ብሎ ማመን የሚያስችል ምክንያት ሲኖረው ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የጽሑፍ ማስታወቂያ በመስጠት፡- ታክስ ከፋዩ ወይም የታክስ እንደራሴው የታክስ ጊዜው የታክስ ማስታወቂያ ማቅረቢያ ጊዜ ባይደርስም ባለሥልጣኑ በሰጠው ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ የቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያ እንዲያቀርብ፣ እና በቅድሚያ ታክስ ማስታወቂያው የተመለከተውን ታክስ ባለሥልጣኑ በሰጠው ማስታወቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ እንዲከፍል፣ ሊያዝ ይችላል፡፡ • ታክስ ከፋዩ ከአንድ የታክስ ዓይነት በላይ የሚመለከተው ከሆነ ይህ አንቀጽ ለእያንዳንዱ ታክስ በተናጠል ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
  • 23. 23 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ስለ ሠነዶች (የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ አንቀጽ 17-2ዐ) • መዝገብ የመያዝ ግዴታዎች ይህ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አንቀጽ የገቢ ግብር አዋጁ 979/2008 አንቀጽ 82 ላይ የተደነገገውን ለማስተዳደር የሚረዳ ነው፡፡ • ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል አንድ ታክስ ከፋይ በታክስ ሕግ መያዝ ያለባቸውን ሰነዶች በኤሌክትሮኒክ መልክ ጨምሮ የመያዝ ግዴታ ያለበት ሲሆን እነዚህም ሰነዶች የሚያዙት፡ 1/በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ፣ 2/በኢትዮጵያ ውስጥ፤ እና 3/የታክስ ከፋዩን የታክስ ግዴታ በግልጽ ለማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ፣ መሆን አለበት፡፡ • በታክስ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር አንድ ታክስ ከፋይ ከላይ የተመለከቱትን ሰነዶች ከሚከተሉት ረጅም ለሆነው ጊዜ ይዞ የማቆየት ግዴታ አለበት፡- 1/በንግድ ሕግ ለተወሰነው የሰነድ መያዣ ጊዜ ርዝማኔ /አዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀጽ 66 “ማንኛውንም የሒሣብ መዝገቦችና የሒሣብ ሰነዶች የመጨረሻው ጽህፈት ከተፃፈባቸው ቀን ጀምሮ ወይም ሰነዶቹ ከተፃፋበት ቀን አንስቶ ወደፊት ላሉት 10 ዓመታት ድረስ ጠብቆ ማኖር ይገባል” ፣ ወይም 2/ሰነዶቹ አግባብነት በሚኖራቸው የታክስ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ ለባለሥልጣኑ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ለአምስት ዓመታት፣ ነገር ግን በአዋጁ መሠረት ለሚደረግ ክርክር ወይም ከላይ ከተመለከተው ጊዜ በፊት ተግባራዊ በሆነ ሕግ መሠረት ለሚደረግ ክርክር ሰነዱ የሚያስፈልግ ሲሆን ታክስ ከፋዩ ሁሉም ክርክሮች እስከሚጠናቀቁ ጊዜ ድረስ ሰነዱን ይዞ የማቆየት ግዴታ አለበት፡፡ • ሰነዱ በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ ካልቀረበ በባለሥልጣኑ በጹሁፍ በሚሰጥ ማስታወቂያ በሚወሰነው ጊዜ ውስጥ ሰነዱ በባለሥልጣኑ ተቀባይነት ባለው ተርጓሚ በታክስ ከፋዩ ወጪ ወደ አማርኛ ወይም ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ ተተርጉሞ እንዲቀርብ ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩን ሊያዘው ይችላል፡፡ • የሂሣብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 176/2014 በዝርዝር ይመልከቱ፡፡ • የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 102 ሰነዶችን ባለመያዝ የሚጣል ቅጣትን ደንግጓል፡፡
  • 24. 24 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ሪፖርት ማድረግ (Reporting) በአግባቡ የቀረበ የታክስ ማስታወቂያ • ተቃራኒ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም ቀርቧል የተባለ የታክስ ማስታወቂያ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ፈቃድ እንደቀረበ ይቆጠራል፡፡ ሰነዶችን ስለመመርመር • በታክስ ሕግ መሰረት ሰነዶችን እንዲይዝ የሚገደድ ታክስ ከፋይ ሰነዱን ይዞ እንዲቆይ በሚጠበቅበት በማንኛውም ምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ሰነዶቹን ለባለሥልጣኑ ምርመራ ዝግጁ የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡ የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች • ባለሥልጣኑ፡- በማናቸውም ሁኔታ ታክስ ከፋዩ ዜሮ መጠንን ጨምሮ ለታክስ ጊዜው መክፈል የሚገባው የታክስ መጠን በትክክል የተሰላ መሆኑን፣ ለማረጋገጥ በሚያገኘው ማስረጃ መሠረት ማንኛውንም የታክስ ስሌት (“የመጀመሪያው የታክስ ስሌት” ተብሎ የሚጠቀስ) በመለወጥ ፣ በመቀነስ ወይም በመጨመር ሊያሻሽል ይችላል፡፡ • አግባብነት ባለው የታክስ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር፣ ባለሥልጣኑ ማንኛውንም የታክስ ስሌት፡- 1) በማንኛውም ጊዜ በታክስ ከፋዩ ወይም በታክስ ከፋዩ ስም የማጭበርበር ድርጊት ሲፈጸም ወይም በከፍተኛ ሁኔታ ወይም በማወቅ የተፈፀመ የቸልተኝነት ድርጊት ሲኖር፣ ወይም 2) በሌላ በማናቸውም ሁኔታ፡- ታክስ ከፋዩ በራሱ የሚያሰላው የታክስ ስሌት ሲሆን ታክስ ከፋዩ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 5(አምስት) ዓመት ውስጥ፣ ለሌላ ማንኛውም የታክስ ስሌት ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ከሰጠበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 5(አምስት) ዓመት ውስጥ፣ ሊያሻሽል ይችላል፡፡
  • 25. 25 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ታክስ ከፋዩ ራሱ ያዘጋጀው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል ስለሚቀርብ ማመልከቻ • የራሱን የታክስ ስሌት ያዘጋጀ ታክስ ከፋይ ያቀረበውን በራስ የተዘጋጀ የታክስ ማስታወቂያ ባለሥልጣኑ እንዲያሻሸልለት ለባለሥልጣኑ ሊያመለክት ይችላል፡፡ በዚህ መሠረት የሚቀርበው ማመልከቻ፣ ታክስ ከፋዩ ራሱ አዘጋጅቶ ባቀረበው የታክስ ማስታወቂያ ላይ ሊደረጉ ይገባል ብሎ የሚያምንባቸውን ማሻሻያዎችን እና ማሻሻያዎቹን ማድረግ አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያቶች መግለጽ፣ እና • ታክስ ከፋዩ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 5 /አምስት ዓመት/ ውስጥ መቅረብ፣ ይኖርበታል፡፡ • በዚህ ድንጋጌ መሠረት ማመልከቻ ሲቀርብለት ማመልከቻው በቀረበለት በ120 (አንድ መቶ ሃያ) ቀናት ውስጥ ባለሥልጣኑ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት በታክስ ከፋዩ ተዘጋጅቶ የቀረበው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል መወሰን ወይም ማመልከቻውን ውድቅ ማድርግ አለበት፡፡ • ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ ራሱ ያቀረበው የታክስ ስሌት እንዲሻሻል የወሰነ እንደሆነ፣ የታክስ ስሌት ማሻሻያው ባለስልጣኑ የታክስ ከፋዩ ኪሣራ በትክክል የተሰላ መሆኑን፣ ታክስ ከፋዩ በታክስ ጊዜው የከፈለው የግብዓት ተጨማሪ እሴት ታክስ በትክክል የተሰላ መሆኑን እና በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ታክስ ከፋዩ ዜሮ መጠንን ጨምሮ ለታክስ ጊዜው መክፈል የሚገባውን የታክስ መጠን በትክክል የተሰላ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚያገኘው ማስረጃ መሰረት ማንኛውንም የመጀመሪያ የታክስ ስሌት ተብሎ የሚጠቀሰውን በመለወጥ፣ በመቀነስ፣ ወይም በመጨመር ሊያሻሽል ይችላል፡ • ይህ ታክስ ከፋዩ የሚያቀርበውን የራስ ታክስ ስሌት እንዲሻሻል ስለሚፈቀድበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 144/2011 የሚፈጸም ይሆናል፡፡ በዚህ መመሪያ በ3ምክንያቶች ማሻሻያው ይከለከላል፡ ነገር ግን እነዚህ ቢኖሩም ባለስልጣኑ በራሱ አነሣሽነት የተሻሻለ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ሊሰጥ ይችላል፡፡
  • 26. 26 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ከታክስ ጋር በተገናኘ የሚፈጠር አለመግባባት /Disputes/ - እንዴት እንፈታቸዋለን? የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 52-60/ በዚህ አዋጅ ከታክስ ጋር በተገናኘ የሚፈጠር አለመግባባት በሚፈታበት አግባብ በተቀመጠ ክፍል /የአዋጁ ክፍል ዘጠኝ/ በተደነገገው ሥነ-ሥርዓት መሰረት ካልሆነ በስተቀር የታክስ(የተሻሻለ)ወይም ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል ውሳኔ ወሳኝ እና የመጨረሻ በመሆኑ በማናቸውም ሁኔታ በኮሚሽኑ ወይም በፍርድ ቤት ወይም በሌላ የዳኝነት ሥነ ሥርዓት ተቃውሞ ሊቀርብበት አይችልም፡፡ ውሳኔ ላይ ስለሚቀርብ የቅሬታ ማስታወቂያ  የውሳኔው ማስታወቂያ በደረሰው በ21 ቀናት ውስጥ የቅሬታ ማስታወቂያ በጽሑፍ ማቅረብ ይችላል፡፡  ቅሬታ የቀረበበት የታክስ ውሳኔ በተሻሻለ የታክስ ስሌት ላይ ከሆነ የታክስ ከፋዩ የተሻሻለውን የታክስ ስሌት የመቃወም መብት የመጀመሪያውን የታክስ ስሌት በመለወጥ፣በመቀነስ ወይም በመጨመር በተደረገው ማሻሻያ ላይ ብቻ የተገደበ ይሆናል፡፡  በታክስ ከፋይ የቀረበ የቅሬታ ማስታወቂያ በአግባቡ እንደቀረበ የሚቆጠረው ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ብቻ ነው፡- ሀ) የቅሬታ ማስታወቂያው ታክስ ከፋዩ የታክስ ውሳኔውን የሚቃወምበትን ምክንያቶች፣ ታክስ ከፋዩ ውሳኔውን ለማስተካከል ሊደረጉ ይገባል ብሎ የሚያምንባቸውን ማሻሻያዎች እና እነዚህን ማሻሻያዎች ማድረግ አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያቶች በትክክል የሚገልጽ ከሆነ፣ ለ) ቅሬታው ከታክስ ስሌት ጋር የተገናኘ ከሆነ ታክስ ከፋዩ በታክስ ስሌቱ መሠረት መከፈል ያለበትን እና በቅሬታ ማስታወቂያው ተቃውሞ ያላቀረበበትን ታክስ የከፈለ እንደሆነ ነው፡፡ ሐ) በታክስ ውሳኔው ላይ ቅሬታ ቢኖረውም ታክሱን ከፍሎ የቅሬታ ማስታወቂያ ማቅረብን የመረጠ ከሆነ የተወሰነበትን ታክስ ከከፈለ ነው፡፡ • የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ከማለፉ በፊት ታክስ ከፋዩ በታክስ ውሳኔ ላይ የቅሬታ ማስታወቂያ የሚያቀርብበት ጊዜ እንዲራዘምለት ለባለሥልጣኑ የጽሑፍ ማመልከቻ ማቅረብ ይችላል፡፡ ባለሥልጣኑ፡- ሀ) ታክስ ከፋዩ በኢትዮጵያ ውስጥ ያልነበረ በመሆኑ፣ በህመም ምክንያት ወይም በሌላ አጥጋቢ ምክንያት በተወሰነው ጊዜ ውስጥ የቅሬታ ማስታወቂያውን ማቅረብ አለመቻሉ፣ እና ለ) የቅሬታ ማስታወቂያውን ለማቅረብ በታክስ ከፋዩ በኩል ምክንያታዊ ያልሆነ መዘግየት አለመኖሩን፣ ሲያምንበት የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜው ካበቃበት ቀን ጀምሮ ከአሥር ቀናት ላልበለጠ ጊዜ ሊያራዝም ይችላል፡፡
  • 27. 27 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ውሳኔ ላይ ስለሚቀርብ የቅሬታ ማስታወቂያ… • ባለሥልጣኑ በሥራ ክፍሉ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበውን ቅሬታ በሙሉ ወይም በከፊል በመቀበል ወይም ውድቅ በማድረግ ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን ውሳኔውም በቅሬታ ላይ የተሰጠ ውሳኔ” ተብሎ ይጠቀሳል፡፡ • ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ ቅሬታ ካቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 180 ቀናት ውስጥ በቅሬታው ላይ ውሳኔ ካልሰጠ ታክስ ከፋዩ ይግባኙን ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ማቅረብ ይችላል እንዲሁም ይግባኝ ሊቀርብበት በሚችል ውሳኔ ላይ ቅር የተሰኘ ታክስ ከፋይ የይግባኝ ማስታወቂያውን ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ሊያቀርብ ይችላል፡፡  በታክስ ስሌት ላይ ከቀረበ ቅሬታ ጋር በተገናኘ በታክስ ከፋይ ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የሚቀርብ የይግባኝ ማስታወቂያ በአግባቡ ቀርቧል ሊባል የሚችለው፡-በክርክር ላይ ያለ ታክስ 50% የተከፈለ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡  በክርክር ላይ ያለ ታክስ ከታክሱ ጋር በተገናኘ ሊከፈል የሚገባውን ቅጣትና የዘገየ ክፍያ ወለድን አይጨምርም፡፡ • ኮሚሽኑ በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ግብር ከፋይ የኮሚሽኑ የውሳኔ ማስታወቂያ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ የይግባኝ ማስታወቂያውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ • የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ እንዲራዘምለት በጽሑፍ ማመልከቻ ለሚጠይቅ ግብር ከፋይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጊዜውን ሊያራዝመው ይችላል፡፡ • በታክስ ስሌት ላይ ከቀረበ ቅሬታ ጋር በተገናኘ በታክስ ከፋይ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርብ የይግባኝ ማስታወቂያ በአግባቡ ቀርቧል ሊባል የሚችለው በክርክር ላይ ያለ ታክስ 75% የተከፈለ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ • ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚቀርበው በሕግ ጉዳዮች ላይ ብቻ ሲሆን የይግባኝ ማስታወቂያውም በቀረበው ይግባኝ የሚነሱትን የሕግ ጉዳዮች መግለጽ አለበት፡፡ • የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ግብር ከፋይ የፍርድ ቤቱ የውሳኔ ማስታወቂያ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ የይግባኝ ማስታወቂያውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡
  • 28. 28 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ታክስ/ግብር መክፈል (Payment) ታክስን ስለመሰብሰብና ማስከፈል / የታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 30-48/ ታክስ ለመንግሥት የሚከፈል ስለመሆኑ • በታክስ ሕግ መሠረት በታክስ ከፋዩ ሊከፈል የሚገባውና የመክፈያ ጊዜው የደረሰ ታክስ ለመንግሥት የሚከፈል ዕዳ ስለሆነ ለባለሥልጣኑ መከፈል አለበት፡፡ • በኤሌክትሮኒክስ አከፋፈል ዘዴ ታክስ እንዲከፍል በባለሥልጣኑ የተጠየቀ ታክስ ከፋይ ባለሥልጣኑ ሌላ የአከፋፈል ዘዴ እንዲጠቀም በጽሑፍ ካልፈቀደለት በስተቀር ክፍያውን የሚፈጽመው በኤሌክትሮኒክስ አከፋፈል ዘዴ ይሆናል፡፡ ይህን ባይጠቀምስ? በአዋጁ አንቀጽ 111 መሰረት የኤሌክትሮኒክስ የታክስ ሥርዓትን አለመከተል የሚያስከትለው ቅጣት ይጣልበታል፡፡ • ታክስ ከፋዩ ታክሱን መክፈል ባለበት ጊዜ ካልከፈለ በህጉ ወለድ ይጠየቃል፤ እንዲሁም በአዋጁ አንቀጽ 105 መሰረት የተቀመጠውን ታክስ ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለውን ቅጣት ይቀጣል ፤በተጨማሪም ባለሥልጣኑ ያልተከፈለውን ታክስ ለማስከፈል በሚወስደው እርምጃ ምክንያት ለሚያወጣው ማንኛውም ወጪ ኃላፊ ይሆናል፡፡ • የመክፈያ ጊዜው የደረሰ ታክስ የመክፈያ ጊዜው እንዲራዘም ለባለሥልጣኑ የጽሑፍ ማመልከቻ ሊቀርብ ይችላል፡-  ማመልከቻ በሚቀርብበት ጊዜ ባለሥልጣኑ በቂ ምክንያት መኖሩን ካረጋገጠ ሀ) ለታክስ ከፋዩ የታክስ መክፈያ ጊዜውን ሊያራዝምለት፣ ወይም ለ) ባለሥልጣኑ በሚወሰነው መሠረት ታክሱን በመከፋፈል በተወሰነ ጊዜ ውስጥእንዲከፍል ሊያደርገው፣ ይችላል፡፡  ለቀረበው ማመልከቻ የሰጠውን ውሳኔ የሚገለጽ የጽሑፍ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጠዋል፡፡  ታክሱን በመከፋፈል በተወሰነ ጊዜ ውስጥ እንዲከፍል የተፈቀደለት ታክስ ከፋይ የአንድን ጊዜ ክፍያ ካልከፈለ ታክስ ከፋዩ ክፍያውን ባቆመበት ጊዜ ያለውን ቀሪ ክፍያ በሙሉ እንዲከፍል ባለሥልጣኑ ወዲያውኑ እርምጃ ሊወስድ ይችላል፡፡  በዘገየው ክፍያ ላይ ከመጀመሪያ የታክስ መክፈያ ቀን ጀምሮ የሚታሰብ ወለድ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡ ዝርዝር አፈፃፀሙ በክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ መመሪያ ቁጥር 142/2011 ተመላክቷል
  • 29. 29 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … የአከፋፈል ቅደም ተከተል • ታክስ ከፋዩ የፈፀመው ክፍያ መክፈል ከሚገባው ጠቅላላ የታክስ፣ የቅጣትና የወለድ መጠን ያነሰ በሚሆንበት ጊዜ የተከፈለው ገንዘብ የሚሸፍነው ዕዳ ቅደም ተከተልን በተመለከተ፡- ሀ) በመጀመሪያ ዋናውን የታክስ ዕዳ ለመክፈል፤ ለ) ቀጥሎ ክፍያ ለዘገየበት የሚከፈል ወለድ፣ ሐ) ቀሪው ገንዘብ ለቅጣት መክፈያ ይውላል፡፡ • ከአንድ በላይ የታክስ ዕዳ የሚፈለግበት ግብር ከፋይ ክፍያው የሚሸፍነው ዕዳ ቅደም ተከተል ዕዳው በተፈጠረበት ጊዜ ቅደም ተከተል መሠረት ይሆናል ፡፡ ለታክስ አከፋፈል የሚቀርብ ዋስትና • ባለሥልጣኑ የመንግሥትን ገቢ ለመጠበቅ አስፈላጊ መስሎ ሲታየው አስፈላጊ ነው በሚለው መጠንና አኳኋን ታክስ ከፋዩ ዋስትና እንዲያቀርብ ሊያስገድደው ይችላል፡፡ ታክስ ከፋዩ ዋስትና እንዲያቀርብ የሚጠየቀውም፡- ሀ) የመክፈያ ጊዜው ለደረሰ ወይም የመክፈያ ጊዜው ለሚደርስ ታክስ መክፈያ፣ ወይም ለ) በታክስ ሕግ መሠረት ተመላሽ ለሚጠይቅ ታክስ ከፋይ ቅድመ ሁኔታ ይሆናል፡፡ • በዚህ መሠረት የሚሰጥ ዋስትና ባለሥልጣኑ የሚጠይቃቸው ተገቢ ቅድመ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ ዋስትና ሊሰጥ ይችላል፡፡ • ታክስ ከፋዩ ዋስትና የማቅረብ ግዴታ የሚኖርበት ባለሥልጣኑ፡- ሀ) የሚፈለገው የዋስትና መጠን፣ ለ) ዋስትናው የሚቀርብበትን አኳኋን፣ እና ሐ) ዋስትናው የሚቀርብበትን ቀን የሚገልጽ የጽሑፍ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ የሰጠ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ • ያላቀረበው የዋስትና መጠን የታክስ ከፋዩ ያልተከፈለ ታክስ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህም በታክስ ክሊራንስ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 147/2011 እና በተእታ ተመላሽ አሰጣጥ መመሪያ 148ና ሌሎች የተመላሽ አፈፃፀም መመሪያዎች መሰረት የተመላከቱ መብቶችን ያዘገያል/ያሣጣል፤
  • 30. 30 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ለዘገየ ክፍያ የሚከፈል ወለድ/አ.37/ • በታክስ መክፈያ ጊዜው ወይም ከዚያ በፊት ታክሱን ያልከፈለ ታክስ ከፋይ ታክሱ መከፈል ከነበረበት ቀን ጀምሮ ተከፍሎ እስካለቀበት ቀን ድረስ ባልተከፈለው መጠን ላይ ለዘገየው ክፍያ ወለድ የመክፈልግዴታ አለበት፡፡ • የዘገየ ክፍያ የወለድ መጣኔ በንግድ ባንኮች ሥራ ላይ በዋለው ከፍተኛው የማበደሪያ ወለድ መጣኔ ላይ 15% (አሥራ አምስት በመቶ) ተጨምሮበት ይሆናል፡፡ • በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 105 መሠረት ታክስን በመክፈያ ጊዜው ባለመክፈል ከሚጣለው ቅጣት በተጨማሪ ይሆናል፡፡ • በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ በነጠላ ወለድ የሚሰላ ሲሆን የሚታሰበውም በየቀኑ ይሆናል፡፡ • ታክስ ከፋዩ የታክስ ዕዳ የታክስ ስሌት ማስታወቂያን እስከተሰጠበት ቀን ድረስ መክፈል የሚጠበቅበትን የዘገየ ክፍያ ወለድን ጨምሮ በማስታወቂያው የተመለከተውን የታክስ ዕዳ በሙሉ በማስታወቂያው በተገለጸው የመክፈያ ቀን የከፈለ ከሆነ ማስታወቂያው በተሰጠበት እና ክፍያው በተፈፀመበት መካከል ላለው ጊዜ የዘገየ ክፍያ ወለድ አይታሰብም፡፡ • ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ በሚከፈል ታክስ ወይም በሁለተኛ ደረጃ ኃላፊነት በሚከፈል ታክስ ላይ የሚታሰብ የዘገየ ክፍያ ወለድ መከፈል ያለበት ይኸው ኃላፊነት ባለበት ሰው ብቻ በመሆኑ ከሌላ ማንኛውም ሰው ሊጠየቅ አይችልም፡፡ • በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ ጠቅላላ መጠን ከታክስ ከፋዩ የታክስ ዕዳ ሊበልጥ አይችልም፡፡
  • 31. 31 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል • ማንኛውም ታክስ ከፋይ ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ እንደሆነ ባለሥልጣኑ ያልተከፈለውን ታክስ እና ታክሱን ለማስከፈል የሚወሰደው እርምጃ የሚያስከትለውን ወጪ ማስከፈል እንዲቻል በታክስ ከፋዩ ሀብት ላይ የባለሥልጣኑን የዋስትና መብት እንዲመዘግብ ንብረቱን ለመዘገበው አካል እንደሚያመለክት የሚገልጽ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጣል፡፡ • ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ ማስታወቂያው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ታክሱን ያልከፈለ እንደሆነ፣ ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ በሰጠው ማስታወቂያ የተመለከተው የታክስ ከፋዩ ሀብት ላልተከፈለው ታክስ እና ታክሱን ለማስከፈል ለሚደረግ ወጪ በዋስትና እንዲያዝ ንብረቱን ለመዘገበው አካል የጽሁፍ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ • ባለሥልጣኑ ታክስ የሚፈለግበት ሰው ሀብት በዋስትና ተይዞ እንዲቆይ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ መዝጋቢው ባለሥልጣን ሀብቱ በዋስትና እንዲያዝ የደረሰውን የጽሑፍ ትዕዛዝ ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይጠይቅ እንደማንኛውም በሀብቱ ላይ እንዳለ የንብረት መያዣ ወይም የዋስትና ሰነድ ይመዘግባል፤ የተረካቢዎች ግዴታዎች • ማንኛውም ተረካቢ የአንድን ታክስ ከፋይ ሀብት በኢትዮጵያ ውስጥ ተረካቢ ሆኖ ከተሾመ ወይም ሀብቱ በይዞታው ሥር ከገባ ከሁለቱ ከሚቀድመው ጊዜ ጀምሮ ባሉት አሥራ አራት ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ በጽሑፍ ማሳወቅ አለበት፡፡ • ባለሥልጣኑ ሀብቱ በተረካቢው ቁጥጥር ሥር ባለው ታክስ ከፋይ ያልተከፈለውን የታክስ ዕዳ እና ወደፊት የሚከፈለውን የታክስ መጠን በመወሰን የጽሑፍ ማስታወቂያ በደረሰው በ 30 ቀናት ውስጥ ለተረካቢው ማሳወቅ አለበት፡፡ • ተረካቢው ሀ) ከባለሥልጣኑ አስቀድሞ ፈቃድ ካላገኘ በስተቀር በእጁ የሚገኘውን የታክስ ከፋዩን ሀብት ማስታወቂያ ከባለስልጣኑ ተሰጥቶት የ30 ቀናት ጊዜ ከማለፍ በፊት መሸጥ ወይም በማናቸውም ሁኔታ ማስተላለፍ አይችልም፡፡ ለ) ከሀብቱ ሽያጭ ገንዘብ ላይ ባለሥልጣኑ የገለጸውን የታክስ መጠን ወይም ባለሥልጣኑ የተስማማበትን የታክስ መጠን ቀንሶ ማስቀመጥ አለበት፡፡ እንዲሁም ሐ) የሀብቱ ባለቤት በሆነው ታክስ ከፋይ መከፈል ላለበት ታክስ ከሀብቱ ሽያጭ ገቢ ተቀንሶ መቀመጥ ባለበት የገንዘብ መጠን ልክ በግል ተጠያቂ ይሆናል፡፡ • ሆኖም ተረካቢው እንዲከፍል ከተጠየቀው ታክስ በማስቀደም የሚከተሉትን ክፍያዎች ከመፈፀም አይከለክለውም፡- ሀ) በሕግ የቅድሚያ መብት ያለውን ዕዳ፣ ለ) የተረካቢውን አበል ጨምሮ ተረካቢው በተረካቢነት ችሎታው የሚያወጣቸውን ወጪዎች፣
  • 32. 32 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል… ሀብትን ስለመያዝ /41/ • ባለሥልጣኑ ታክሱን በመክፈያ ጊዜው ላልከፈለ ታክስ ከፋይ የሚፈለግበትን ታክስ ማስጠንቀቂያ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ካልከፈለ የታክስ ከፋዩ ሀብት እንዲያዝ ትዕዛዝ የሚሰጥ መሆኑን የሚገልጽ ማስጠንቀቂያ ለታክስ ከፋዩ ሊሰጠው ይችላል፡፡ • ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ የሚፈለግበትን ታክስ የሚከፍል ለመሆኑ ስጋት መኖሩን ካረጋገጠ የመያዣ ትዕዛዙን ወዲያውኑ ሊሰጥ ይችላል፡፡ • በተሰጠው ማስጠንቀቂያ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ታክሱን ካልከፈለ ወይም ስጋት መኖሩ ሲረጋገጥ ባለሥልጣኑ የመያዣ ትዕዛዙን ለታክስ ከፋዩ ሊሰጥ ወይም የታክስ ከፋዩን ሀብት በይዞታው ሥር ባደረገ በማንኛውም ሰው ላይ ሊያስተላልፍ ይችላል፡፡ • የመያዣ ትዕዛዙ ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት በስተቀር በማንኛውም የታክስ ከፋዩ ሀብት ላይ ተፈጻሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ሀ) በሀብቱ ላይ የቀደምትነት መብት ባላቸው የገንዘብ ጠያቂዎች በተያዘ ንብረት፣ ለ) በማናቸውም የፍርድ ሂደት ዕገዳ በተደረገበት ወይም የአፈፃፀም ትአዛዝ በተሰጠበት ንብረት፣ ሐ) በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ሊታገድ በማይችል ንብረት፣ • በታክስ ከፋዩ ንብረት ላይ የመያዣ ትዕዛዝ ከተሰጠ ወይም የሚሰጥ ከሆነ ባለሥልጣኑ በጽሑፍ በሚሰጥ ማስታወቂያ የሚያዘውን ሀብት በሚመለከት በማስረጃነት ሊያገለግል የሚችል ማንኛውንም ሰነድ ወይም መግለጫ የያዘ ማንኛውም ሰው ይህን ሰነድ ወይም መግለጫ ለባለሥልጣኑ እንዲያቀርብ ሊጠይቀው ይችላል፡፡ • ባለሥልጣኑ የታክስ ከፋዩን ንብረት በሚይዝበት ጊዜ የሚከተሉትን ነጥቦች የያዘ ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ይሰጠዋል፡- ሀ) የተያዘውን ንብረት እና ያልተከፈለውን የታክስ መጠን፣ ለ) ታክስ ከፋዩ በማስታወቂያው በተገለጸው ሀብቱ ተይዞ በሚቆይበት ጊዜ ውስጥ የሚፈለግበትን ታክስ የማይከፍል ከሆነ ሀብቱን እንደሚሸጠው፤
  • 33. 33 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ያልተከፈለን ታክስ ለማስከፈል… • በፋይናንስ ተቋማት የተቀመጠ ገንዘብ እና ንብረት ይዞ ለማቆየት ይቻላል/42/ • ያልተከፈለን ታክስ ከሦስተኛ ወገኖች ለማስከፈል ይቻላል/43/ • ከሀገር መውጣትን ለመከልከል የሚሰጥ ትዕዛዝ ሊተላለፍ ይችላል (ታክስ ከፋዩ ወይም የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም በአንድ ኩባንያ ወሳኝ ድምጽ ያለው አባል) /44/ • የንግድ ድርጅትን ለጊዜው ለማሸግ ይችላል /45/ አንድ ታክስ ከፋይ በተደጋጋሚ፡- ሀ) በግብር ሕግ መሠረት የሚፈለግበትን ሰነድ ሳይዝ ሲቀር፣ወይም ለ) ታክሱን በመክፍያ ጊዜው ሳይከፍል ሲቀር ይሆናል፡፡ • አንድ ታክስ ከፋይ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራ ጋር በተገናኘ ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ ያለበት እንደሆነ እና የንግዱን ሀብቶች በሙሉ ወይም በከፊል ግንኙነት ላለው ሰው ያስተላለፈ እንደሆነ ከንግዱ ሀብት ጋር ተያይዞ ያልተከፈለውን ዕዳ ሀብቱ የተላለፈለት ሰው የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል፡፡ ይህ ግን ባለሥልጣኑ የተላለፈውን የታክስ ዕዳ በሙሉ ወይም በከፊል ከሀብት አስተላላፊው ላይ እንዳይጠይቅ አያግደውም፡፡ • አንድ ድርጅት ታክሱን በመክፈያው ጊዜ ውስጥ ያልከፈለ እንደሆነ ታክሱ ባልተከፈለበት ጊዜ ወይም ታክሱ ከመከፈሉ በፊት ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ሥራ አስኪያጅ የነበረ ማንኛውም ሰው ላልተከፈለው ታክስ ከድርጅቱ ጋር የአንድነትና የነጠላ ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡  ከላይ የተጠቀሰው በሚከተሉት ሁኔታዎች ተፈፃሚ አይሆንም፡- ሀ) ድርጅቱ የሚፈለግበትን ግብር ሳይከፍል የቀረው ከሥራ አስኪያጁ ፈቃድ ወይም ዕውቀት ውጭ የሆነ እንደሆነ፣ እና ለ) ሥራ አስኪያጁ ድርጅቱ ግብር ላለመክፈል የሚያደርገውን ጥረት ለመከላከል ተገቢውን ትጋት አሳይቶ የሆነ እንደሆነ ነው፡፡
  • 34. 34 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ለታክስ ክፍያዎች የሚሰጥ ማካካሻ /49-50/ • ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ ለቀረ ታክስ እና በቅድሚያ ለተከፈለ ታክስ ሊገኝ የሚገባ ማካካሻ በታክስ ዓመቱ ከሚፈለግ የገቢ ግብር ዕዳ በሚበልጥበት ጊዜ፤ በብልጫ የታየውን ገንዘብ በሚከተለው ቅደም ተከተል ሥራ ላይ ይውላል፡፡ ሀ) በመጀመሪያ በገቢ ግብር አዋጅ መሠረት ለሚፈለግ ማንኛውንም ታክስ ፤ ለ) ቀሪው ታክስ ከፋዩ በሌላ በማንኛውም የታክስ ሕግ የሚፈለግበትን ታክስ ለመክፈል ይውላል፡፡ ሐ) ከዚህ ሁሉ ተራፊ ገንዘብ ካለም ታክስ ከፋዩ በጽሑፍ የተመላሽ ጥያቄ ካቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 90 ቀናት ውስጥ ለታክስ ከፋዩ ይመለስለታል፡፡ • ታክስ ከፋዩ በጽሑፍ ስምምነቱን ከገለጸ ወደፊት ለሚመጣ ማንኛውም የታክስ እዳ መክፈያነት ሊሸጋገር ይችላል፡፡ • ባለሥልጣኑ ተራፊውን ገንዘብ ለታክስ ከፋዩ ካልከፈለ፤ 90ናኛው ቀን ካለቀ ጀምሮ ተራፊው ገንዘብ እስከሚመለስበት ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ታክስ ከፋዩ ወለድ የማግኘት መብት አለው፡፡ • ነገር ግን ባለሥልጣኑ ታክስ በስህተት ተመላሽ ያደረገ እንደሆነ ታክስ ከፋዩ በባለሥልጣኑ ሲጠየቅ በመጠየቂያ ሰነድ በተጠቀሰው ቀን በስህተት የተመለሰለትን ገንዘብ ለባለሥልጣኑ መልሶ መክፈል አለበት፡፡ • ተመላሽ በሚጠይቀው ታክስ ከፋይ አሳሳችነት ገንዘብ በስህተት የተመለሰ እንደሆነ ታክስ ከፋዩ ገንዘቡ በስህተት በተመለሰበትና በስህተት የተመለሰው ገንዘብ ተመልሶ ለባለሥልጣኑ በተከፈለበት ቀን መካከል ላለው ጊዜ ወለድ የመክፈል ኃላፊነት አለበት፡፡
  • 35. 35 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ከባድ ችግር ሲያጋጥም ስለሚሰጥ የታክስ ምህረት /51/ • ይህ ተፈጻሚ የሚሆነው ሚኒስትሩ፡- ሀ) ባልተጠበቀ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ጥፋት ምክንያት ወይም ከታክስ ከፋዩ ቸልተኝነት ወይም ማንኛውም ጥፋት ጋር ባልተገናኘ ሁኔታ የተፈጠረ ከባድ የግል ችግር ምክንያት ታክስ ከፋዩ የሚፈለግበትን ታክስ በሙሉ እንዲከፍል ማድረግ የማይቋቋመው ከባድ ችግር የሚያስከትልበት መሆኑን፣ ወይም ለ) በታክስ ከፋዩ ሞት ምክንያት ታክስ ከፋዩ መክፈል የሚኖርበትን ታክስ በሙሉ እንዲከፈል ማድረግ በታክስ ከፋዩ ጥገኞች ላይ ከባድ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ሲያምንበት ነው፡፡ • በዚህ ጊዜ ሚኒስትሩ ታክስ ከፋዩ መክፈል የሚኖርበትን ታክስና ከዚህ ታክስ ጋር በተገናኘ ለዘገየ ክፍያ የሚጠየቀውን ወለድ በሙሉ ወይም በከፊል እንዳይከፈል ሊፈቅድ ይችላል፡፡ • የዚህ አይነት የታክስ ዕዳ ምህረት ሊደረግ የሚችለው የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ በሚወሰን የገንዘብ መጠን ልክ ይሆናል፡፡ በደንቡ አንቀጽ 7 መሰረት በዚህ ሁኔታ የሚሰጠው የታክስ እና የዘገየ ክፍያ ወለድ ምህረት ለሚንስትሩ የተሰጠው የገንዘብ ጣሪያ 10,000,000/አስር ሚሊየን ብር/ ነው፡፡ • ሚኒስትሩ በዚህ መሠረት ምህረት የተሰጠበትን እያንዳንዱን የታክስ ዕዳ እና የወለድ መጠን እና ምህረት የተሰጠበትን ምክንያት መዝግቦ በመያዝ በየስድስት ወሩ ለዋናው ኦዲተር ሪፖርት ማቅረብ አለበት፡ (ለግልፅነት እና ለቁጥጥር) • የተጣሉ አስተዳደራዊ መቀጫዎች በመቀጫ አነሳስ መመሪያ 137/2010 መሰረት እና በእዳ ምህረት መመሪያ 64/2012 መሰረት ይፈፀማሉ/ይነሳሉ • በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ንብረታቸው ለወደመባቸው ባለሐብቶች ድጋፍ ስለሚደረግበት ሁኔታ የወጣ መመሪያ 69/2013
  • 36. 36 ከግብር ከፋዮች የሚጠበቅ … ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት /የገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ 88-93/ • በፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ከተከፋይ ሒሳብ ላይ በአዋጁ በተመለከተው የግብር ማስከፈያ መጣኔ መሰረት ተቀናሽ እየተደረጉ ለግብር ባለስልጣኑ መከፈል ያለባቸው የግብር ዓይነቶችና ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ ገቢ የማድረግ ግዴታ በህግ የተጣለባቸው ሰዎች በጸደቀው ቅጽ መሰረት ለባለስልጣኑ የማስታወቅና ግብሩን አብሮ የመክፈል ግዴታ አለባቸው፤ ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው 1  ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር  በሌላ ቀጣሪ ተቀናሽ ያልተደረገ ከአንድ በላይ ቀጣሪዎች ባሉት ተቀጣሪ ከሚከፈለው ጠቅላላ ክፍያ ላይ የሚከፈል ግብር በሰንጠረዠ “ሀ” በተመለከተው የማስከፈያ መጣኔ መሰረት  የተቀጣሪው ቀጣሪ  ከተቀጣሪው ቀጣሪዎች አንዱ ወይም ሌላው (አስቀድሞ መረጃ ያገኘው)
  • 37. 37 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት … ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈ ያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው 2 በኢትዮጵያ ነዋሪ ባልሆኑ ሰዎች ከሚፈጸም፣  የወለድ ክፍያ  የትርፍ ድርሻ ክፍያ  የንዑስ ስራ ተቋራጭ ክፍያ  የሮያልቲ ክፍያ  የስራ አመራር ክፍያ  የቴክኒክ አገልግሎት ክፍያ  የመድን አርቦን ክፍያ (በውጭ አገር ለሚኖሩ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የሚከፈል አርቦን)  ወደውጭ የሚላክ ትርፍ  በአዝናኝ የሚፈጸም ክፍያ  ያልተከፋፈለ ትርፍ 10% 10% 10% 5% 15% 15% 5% 10% 10% 10% - ወለድ የሚከፈለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት - የትርፍ ድርሻ የሚያከፋፍለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት - ዋናው ስራ ተቋራጭ - የሮያልቲ ክፍያ የሚፈጽመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት - የስራ አመራር ክፍያ የሚፈጽመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም ኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት - የቴክኒክ ክፍያ የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት (ያለው ነዋሪ ያልሆነ ሰው) - የኢንሹራንስ አርቦን ክፍያ የሚፈጽም የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጰያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት - ትርፍን ወደ ውጭ የሚልከው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት - ክፍያውን የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት (ያለው ነዋሪ ያልሆነ ሰው) - ያልተከፋፈለ ትርፍ ያለው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው፡፡
  • 38. 38 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት … ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው 3 የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት፤  የትርድ ድርሻ ሲከፍል  ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ  ወለድ ሲከፍል  ሮያልቲ ሲከፍል 10% 10% 10% 5% - ክፍያውን የፈጸመው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነው ሰው ወይም በቋሚነት የሚሰራ ድርጀት 4 ነዋሪ የሆነ ድርጅት የኢትዮጵያ ነዋሪ ለሆነ ሰው፡-  የትርፍ ድርሻ ሲከፍል  ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ 10% - ክፍያ የፈጸመው ወይም ያልተከፋፈለ ትርፍ የያዘው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ድርጀት 5 በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት፡-  ከዲፖዚት ወለድ ሲከፍል  ከሌላ ምንጭ ወለድ ሲከፍል  ወደውጭ ትርፍ ሲልክ  ያልተከፋፈለ ትርፍ ሲይዝ 5% 10% 10% 10% - ክፍያን የፈጸመው ወይም ያልተከፋፈለ ትርፍ የያዘው የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በቋሚነት የሚሰራው ድርጀት
  • 39. 39 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት … ተ. ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው 6 በዕድል ሙከራ አሸናፊ ለሆነ ማንኛውም ሰው የሚፈጸም ክፍያ 15% - ክፍያ የሚፈጽመውና የዕድል ሙከራ ለማጫወት ፈቃድ ያለው ሰው ወይም - (ለአሸናፊው ገንዘቡን የሚከፈለው ሰው) 7 በአገር ውስጥ በሚደረጉ ግብይቶች ከሚፈጸሙ ክፍያዎች  ከ10 ሺህ ብር በላይ ለሆነ የዕቃ ሽያጭ ከሚፈጸም ከፍያ  ከ3000 ብር በላይ የሆነ ማንኛውም የአገልግሎት ክፍያ ሲፈጸም TIN ከቀረበ 2% TIN ካልቀረበ 30% - ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞችን ሳይጨምር ክፍያ የፈጸመ ማንኛውም ድርጀት ፣ የመንግስት መስሪያ ቤት፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጀት ወይም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጀት እንዲሁም ባለስልጣኑ በሚያወጣው መመሪያ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ኃላፊነት የተጣለባቸው ግለሰብ ግብር ከፋዮች፡፡
  • 40. 40 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት … ተ.ቁ የግብር ዓይነት (የክፍያ ዓይነት) የማስከፈያ መጣኔ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብሩን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ የመክፈል ግዴታ ያለበት ሰው 8 በዓለም አቀፍ ድርጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለ የውጭ አገር ኢምባሲ፣ ዲፕሎማቲክ ሚሽን ወይም ሌላ ኮንስለር ተቋም ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ የሚፈጸም ክፍያ  በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት ለሌለውና የኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ  በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ላልሆነ ድርጀት ተቀጥሮ ለሚሰራ ተቀጣሪ የተከፈለ ክፍያ በሰንጠረዥ “ሀ” መሰረት በሰንጠረዠ “ሀ” መሰረት በሰንጠረዠ “ሀ” መሰረት - ግብሩ በቀጣሪው ያልተከፈለ እንደሆነ ክፍያ የተፈጸመበት ተቀጣሪ ራሱ ግብሩን ቀንሶ በማስቀረት በየሶስት ወሩ ለታክስ ባለስልጣኑ ማስገባት አለበት፡፡ - ተቀጣሪው ራሱ - ተቀጣሪው ራሱ
  • 41. 41 “ግብር ለሥልጣኔ የሚከፈል ዋጋ ነው!” አመሰግናለሁ!